TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.4K photos
1.51K videos
215 files
4.12K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#AddisAbaba

በዶ/ር እስራኤል ጥላሁን ግድያ ዙሪያ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክር ምክትል ኮማንደር ማርቆስ ታደሰ ምን አሉ ? #ትርታኤፍኤም

" እጅግ በጣም የሚያሳዝንና ሁላችንንም አንገት ያስደፋ ወንጀል ነው የተፈጠረው።

በ28/03/2016 ለሊት 11 ሰዓት ለቅዳሜ አጥቢያ ቦሌ ክ/ከተማ ልዩ ስፍራው አዲስ ሕይወት የሚባል አካባቢ የተፈፀመ ወንጀል ነው።

ምርመራ መዝገቡ እንደሚነግረን ሟች ዶ/ር እስራኤል ጥላሁን የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ3 36734 አአ ሃሉክስ ፒካፕ እያሽከረከሩ ነበር።

ከኃላ ደግሞ ሌላ ስፖኪዮውን ገጭቶ አመለጠብኝ የሚል ከፍተኛ ክላክስ እያሳማ በፍጥነት የሚያሽከረክር የሰሌዳ ቁጥር ኮድ 3 B28177 የሆነ ተሽከርካሪ ከኃላ እየተከታተለ ነበር።

የወንጀል መከላከል ስራ እንዲሰሩ የተመደቡ ሁለት የፖሊስ አባላት አሉ ፤ ለአንደኛው ፖሊስ ይነግረዋል። ይሄ ፖሊስ እንደሰጠው ቃል ' ምናልባት ወንጀል ፈፅሞ ሊሆን ይችላል በሚል ጎማውን መትቼ አቆመዋለሁ ' በሚል ጥይት ይተኩሳል።

ጥይቷ በጀርባ በኩል የተሽከርካሪውን አካል ቀዳ ገብታ የዶክተሩ ህይወት እንዲጠፋ ምክንያት ሆኗል። እጅግ በጣም አሳዛኝ ድርጊት ተፈፅሟል።

ወዲያው ተጠርጣሪ የፖሊስ አባል በቁጥጥር ስር እንዲውል ተደርጎ ምርመራ እየተጣራ ነው። ከእሱ ጋር ተመድቦ የነበረውን ጨምሮ ስፖኪዮ ተገጨብኝ ያለውን በከፍተኛ ፍጥነት ሲከታተል የነበረውን አሸከርካሪ በቁጥጥር ስር እንዲወል ተደርጎ ምርመራ እየተጣራ ነው።

በማህበራዊ ሚዲያ ' የተሽከርካሪዬን ስፖኪዮ ገጭተህብኛል በሚል ከገቢና ወርዶ አንዳንዱ ፖሊስ ነው ከተገጨው መኪና ወጥቶ በቀጥታ በሽጉጥ የመታው ይላል አንዳንዱ ዳግሞ ባለስልጣን ነው ይላል ' የተለያዩ የሀሰት መረጃዎች ናቸው እየተናፈሱ ያሉት፤ ህብረተሰቡ ለሀሰት መረጃ ጆሮውን መስጠት አይገባውም። "

@tikvahethiopia