TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.4K photos
1.51K videos
215 files
4.12K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Reminder 🛎

#National_Exit_Exam

በመጪው 2015 ዓ/ም መጨረሻ ላይ የመውጫ ፈተና መሰጠት ይጀምራል።

በ2015 ዓ.ም መጨረሻ መተግበር በሚጀምረው የመጀመሪያ ዲግሪ ተመራቂዎች የመውጫ ፈተና ዙሪያ ከሰሞኑን የትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ሳሙኤል ክፍሌ (ዶ/ር) ለአዲስ ዘመን ማብራሪያ ሰጥተው ነበር።

ሚኒስትር ዴኤታው ካነሳሷቸው ሃሳቦች መካከል ዋና ዋናዎቹ የሚከተሉት ናቸው

• የመውጫ ፈተና ምዘና የሚሰጠው ለመጀመሪያ ዲግሪ ተማሪዎች ብቻ ነው።

• በግልም ሆነ በመንግስት የትምህርት ተቋም የሚማር ተማሪ ዲግሪውን የሚያገኘው ምዘናውን ሲያልፍ ብቻ ነው፡፡

• የመውጫ ፈተናው የሚዘጋጅበት፣ የሚያዝበት እና የሚሰራጭበት ስርዓት ከሰው ንክኪ ነጻ ለማድረግ እየተሰራ ነው።

• በየዓመቱ ከ150 እስከ 180 ሺህ በመጀመሪያ ዲግሪ የሚመረቁ ተማሪዎችን ምዘና ለመስጠት የሚያስችል አቅም አለ፡፡

• የሙያ ማኅበራት አቅማቸው ሲጎለብት የሙያ ፈተና ይሰጣሉ፤ የመውጫ ፈተና ሥራን ከመንግስት ይረከባሉ።

• ፈተናውን የሚያሰናዱ ተቋማትና መምህራን ዝግጅት ሥራዎች እስከ ግንቦት 2015 ዓ.ም ይሰራሉ፡፡

• የፈተና አሰጣጥ ሂደቱን በቴክኖሎጂ በመደገፍ ግልጸኝነቱ የተጠበቀ ለማድረግ እየተሰራበት ነው።

@tikvahethiopia @tikvahuniversity
ዳግም የሀገራችንን ስም በዓለም ከፍ ያደሩጉት ወጣቶች !

ላለፉት 6 ተከታታይ ቀናት በኮሎምቢያ ካሊ የዓለም ከ20 ዓመት በታች አትሌቲክስ ሻምፒዮና ሲካሄድ ሰንብቷል።

በዚችም ሀገራችን በ19 አትሌቶች በሁለቱም ፆታ በ10 የውድድር ተግባራት ብቻ ተሳትፋለች።

የአትሌቲክስ ቡድናችን በሻምፒዮናው ፦

🥇6 ወርቅ፣
🥈5 ብር
🥉1 ነሃስ በድምሩ በ12 ሜዳልያዎች በማግኘት ከዓለም ሃገራት አሜሪካንን እና ጃማይካን በመከተል 3ኛ ደረጃን ይዘን አጠናቀናል።

የተመዘገበው ውጤት እስከ ዛሬ ከተካሄዱት የዓለም ከ20 ዓመት በታች አትሌቲክስ ሻምፒዮና የተሳትፎ ታሪካችን ዘንድሮ #ከፍተኛው ውጤት ነው።

ከተሳተፍንበት ውስን የውድድር ተግባራት አንፃር እጅግ የሚያኮራ ውጤት ነው።

ሜዳሊያ ያስመዘገቡ የነገዎቹ የሀገር ተስፋዎች እነማን ናቸው ?

#ወርቅ

🥇ኤርሚያስ ግርማ (800 ሜትር)
🥇መልክነህ አዘዘ (3000 ሜትር)
🥇አዲሱ ይሁኔ (5000 ሜትር)
🥇ሳሙኤል ዱጉና (3000 ሜትር መሰናክል)
🥇 ብርቄ ሀየሎም (1500 ሜትር)
🥇መዲና ኢሳ (5000 ሜትር)

#ብር

🥈ኤርሚያስ ግርማ (1500 ሜትር)
🥈ሳሙኤል ፍሬው (3000 ሜትር መሰናክል)
🥈ፅዮን አበበ (3000 ሜትር)
🥈መልክናት ውዱ (5000 ሜትር)
🥈ሲምቦ አለማየሁ (3000 ሜትር መሰናክል)

#ብር

🥉መሰረት የሻነህ (3000 ሜትር መሰናክል)

እንኳን ደስ አለን አላችሁ !

ይቀላቀሉ : @tikvahethsport
https: //t.iss.one/+VvwzStMNcNHmhK0x

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#ትምህርት_ሚኒስቴር የ2014 12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተናን በ12 ኮድ (በጥያቄ አቀማመጥ ስብጥር) ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ ነው። የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ከዚህ በፊት እንደነበረው በ4 ኮድ (4 የተለያዩ ፈተናዎች/በጥያቄ አቀማመጥ) ሳይሆን እስከ 12 እንዲሆን እየተሰራ መሆኑን የትምህርት ሚኒስትር ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ተናግረዋል። ይህ የፈተና ኩረጃን ለመከላከል ከሚሰሩት ስራዎች መካከል አንዱ…
#NationalExam

የ12ኛ ክፍል ፈተና ከመስከረም 30 ቀን 2015 ጀምሮ ይሰጣል።

የ2014 የትምህርት ዘመን ብሔራዊ 12ኛ ክፍል መልቀቂያ ማጠቃለያ ፈተና ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል።

ፈተናው ከመስከረም 30/2015 ዓ/ም ጀምሮ በመንግስት ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቋል።

የፈተና ደንብ ጥሰቶች #በህግ ያስጠይቃሉም ተብሏል።

የ2014 ዓ/ም ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተናን በዩኒቨርሲቲዎች ከመስጠት ባለፈ የፈተና ኩረጀ እና ስርቆትን ለመከላከል በ12 ኮድ (በጥያቄ አቀማመጥ ስብጥር) ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑ ከቀናት በፊት መገለፁ ይታወሳል።

የትምህርት ሚኒስትር ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ፤ የ12ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ከዚህ በፊት እንደነበረው በ4 ኮድ (4 የተለያዩ ፈተናዎች/በጥያቄ አቀማመጥ) ሳይሆን እስከ 12 እንዲሆን እየተሰራ እንደሚገኝ ገልፀው እንደነበር አይዘነጋም።

ይህ የፈተና ኩረጃን ለመከላከል ከሚሰሩት ስራዎች መካከል አንዱ ሲሆን ለጎን ያሉ ተማሪዎች እርስ በእርስ የሚፈተኑት ፈተና የጥያቄው ዝርዝር (order) በፍፁም የተገናኘ እንዳይሆን ለማድረግ የታሰበ ነው።

@tikvahethiopia @tikvahuniversity
#VistOromia

የቱሪዝም እና ቴክኖሎጂ ሳምንት ከነሐሴ 4 እስከ ነሐሴ 7 በአዲስ አበባ ይካሄዳል።

የኦሮሚያ ቱሪዝም ኮሚሽን ያዘጋጀው "የቱሪዝም እና ቴክኖሎጂ ሳምንት" ከፊታችን ነሐሴ 4 ጀምሮ በአዲስ አበባ ስካይ ላይት ሆቴል እንደሚካሄድ ተገልጿል።

መድረኩ በተለይ ሁለቱን ትልልቅ ዘርፎች አካቶ በማቅረብ በሀገራችን የመጀመሪያው ሲሆን ከመንግስት እንዲሁም ከግል ተቋማት ያሉ የዘርፉ ዋነኛ ተሳታፊዎችን ያሳተፈ ነው።

4 ቀናት በሚቆየው በዚህ መርሐግብር የቱሪዝም ኤግዚቢሽን፤ የቱሪዝም ውይይት መድረክ፤ የቱሪዝም ሃካቶን 2014 (Hackathon 2022)፤ ቱሪዝም ቴክኖሎጂ እና ዲጂታል መፍትሄዎች የሚቀርቡበት ሲሆን በተጨማሪም ከቱሪዝም እና ከመንግስት ቁልፍ ባለድርሻ አካላት ጋር ትስስር ለመፍጠር (Networking) ምቹ ሁኔታን የሚያመቻች መድረክ ነው።

በተለይ ፦

👉 ቱሪዝም፥ ከቴክኖሎጂ ጋር ስላለው ጥልቅ ትስስር፤
👉 ዘርፉ ስላለው ሰፊ የሥራ ዕድል ፈጠራ አቅም፤
👉 በማክሮ ኢኮኖሚ ማዕቀፍ ውስጥ ያለው ድርሻ
👉የትራንስፖርት፣ የመሰረተልማትና የኢንቨስትመንት ልማት ለዘርፉ ስለሚኖረው ሚና የፖናል ውይይት ይካሄዳል ተብሏል።

በተጨማሪ ቱሪዝም ፖሊሲ ላይ ጠቃሚ ግብዓቶች የሚገኙበት ይሆናል ተብሏል።

የኦሮሚያ ቱሪዝም ኮሚሽን ከነሐሴ አራት እስከ ነሐሴ 7 በስካይ ላይት ሆቴል በሚያከናውነው በዚህ ትልቅ ኤግዚቢሽን ላይ ፍላጎቱ ያላቸውና ከዘርፉ ተዋንያን ጋር መገናኘት ለሚፈልጉ በሙሉ በስፍራው ተገኝተው መሳተፍ እንደሚችሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በላከው መረጃ ገልጿል።

@tikvahethiopia
#ደራሽ

በሳምንት ለአምስት ቀናት የሚታየው ተከታታይ ድራማ ፦

በኢትዮጵያ ያለው የፊልም ኢንደስትሪ በተቀዛቀዘበት በዚህ ወቅት በተከታታይ የቴሌቭዥን ድራማዎች ኢንዱስትሪውን ለመነቃቃት ሰፊ ስራዎች እየተሰሩ ይገኛል።

በዘርፉ ላይ ተግዳሮት ሆኖ የቆየውን የአቅም ችግር በመጠኑም ቢሆን በመቅረፍ ለሙያተኞች እንዲሁም ለተመልካቾች ትልቅ እድል ይዞ የመጣው አቦል ቲቪ ተጠቃሽ ነው፡፡

የሀገራችን የፊልም ኢንዱስትሪ ፈተና ውስጥ በገባበት በዚህ ወቅት አቅም ያላቸው ዓለም አቀፍ ተቋማት መቀላቀላቸው ሰፊ የሥራ ዕድል ለሚፈጥረው ለዘርፉ ትልቅ ተስፋን የሚሰጥ ሆኗል።

አቦል ከኤምኔት ቻናሎች አንዱ ሲሆን በአሁኑ ወቅት ከ80 በላይ #የኢትዮጵያ ፕሮዳክሽን ካምፓኒዎች በተለያየ መልኩ አብረው የመስራት ዕድል አግኝተዋል።

አቦል ቴሌቪዥን ለተመልካች ካቀረባቸው ውስጥ '' ደራሽ '' የተሰኘው ተከታታይ የቴሌቭዥን ድራማ አንዱ ሲሆን ከ200 በላይ ባለሞያዎችን በማሳተፍ ከሰኞ እስከ አርብ በተከታታይ ይተላለፋል፡፡

ያንብቡ : https://telegra.ph/ደራሽ-08-03
#የዩኒቨርሲቲ_መምህራን !

በዩኒቨርሲቲ መምህራን ማህበራት በኩል የቀረቡ ጥያቄዎች ፦

• መንግሥትን የደመወዝ ጭማሪ እና የዕርከን ዕድገት እንዲያደርግ ጠይቀዋል።

• ለዩኒቨርሲቲ የአካዳሚክ እና ቴክኒካል ረዳቶች የተሰራውን አዲሱን የስራ ደረጃ ማሻሻያ JEG በተመለከተ ቅሬታ አላቸው።

• የመምህራን የቤት አበልን በተመለከተ በፍጥነት አሁን ያለው የቤት ኪራይ ዋጋ ከግምት አስገብቶ ተሻሽሎ ተግባራዊ እንዲደረገ ጠይቀዋል።

• በመንግስት የተደረገው የደረጃ ማሻሻያ ረጅም ጊዜ በዩንቨርሲቲ ያስተማሩ መምህራንን ልምድ ያላገናዘበ በመሆኑና በመምህራን መካከል በቀጣይ ፍትሀዊ የደምወዝ ልዩነት እንዲኖር ስለማያስችል የደረጃ ማሻሻየው የመምህራንን ልምድ እና ማዕረግ ያገናዘበ እንዲሆን ጠይቀዋል።

• የረዳት ፕሮፌሰር የአካዳሚክ ማዕረግ ዝቅተኛ ተፈላጊ ችሎታ የ3ኛ ዲግሪ መደረጉን በተመለከተ ያለን ቅሬታ አላቸው።

• የአካዳሚክ ቴክኒክ ረዳቶች ዝቅተኛው ተፈላጊ የትምህርት ደረጃ የመጀመሪያ ዲግሪ መሆኑ ላይ አቤቱታ አላቸው።

• የቺፍ ቴክኒካል ረዳት II የትምህርት ደረጃን ፒ ኤችዲ ዲግሪ መሆኑም ላይ አቤቱታ አላቸው።

ጥያቄዎቻችን መልስ ይሰጣቸው እያሉ የሚገኙት መምህራኑ ይህ ካልሆነ እስከ ስራ የማቆም አድማ መምታት ድረስ ዕርምጃ እንደሚወስዱ ገልፀዋል።

👉 ትምህርት ሚኒስቴር ለሪፖርተር ፥ " ጥያቄ እንዳለ እናውቃለን። ነገር ግን አሁን ላይ ለውጦች ለማምጣት ጥናት እየተካሄደ ነው። ከዚህ ባለፈ የምንለው ነገር የለም። የደመወዝ ጉዳይ የትምህርት ሚኒስቴር ብቻ አይደለም የሲቪል ሰርቪስ ጉዳይም ነው "

ያንብቡ : telegra.ph/ETH-08-07-2

@tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የሶማሊያ ፓርላማ ነገ እሁድ ይሰበሰባል። በነገው ስብሰባ በጠቅላይ ሚኒስትር ሀምዛ አብዲ ባሬ የቀረበውን የካቢኔ አባላት ላይ ድምፅ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል። ከቀናት በፊት ጠ/ሚኒስትሩ የቀድሞ " አልሸባብ " ምክትል መሪ ሙክታር ሮቦው የሀይማኖት ጉዳዮች ሚኒስትር ያደረጉበት 26 የካቢኔ አባላት ፓርላማው እንዲያፀድቅላቸው መጠየቃቸው ይታወሳል። @tikvahethiopia
የትላንቱ የጎረቤት ሶማሊያ ፓርላማ ውሎ ምን ይመስል ነበር ?

• 229 ድጋፍ
• 7 ተቃውሞ
• 1 ድምፀ ተአቅቦ

በትላንትናው ዕለት የጎረቤታችን ሶማሊያ ፓርላማ የሀገሪቱ ጠ/ሚ ባቀረቡት የካቤኔ አባላት ላይ ድምፅ ለመስጠት ተሰብስቦ ነበር።

በዚህም ጠ/ሚ ሀምዛ አብዲ ባሬ ያቀረቡትን የካቢኔ አባላት በ229 ድጋፍ፣ በ7 ተቃውሞ ፣ በ1 ድምፀ ተአቅቦ በአብላጫ ድምፅ አፅድቋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ በካቢኔያቸው ያካተቷቸው የቀድሞ የአልሸባብ የሽብር ቡድን ምክትል መሪ የነበሩት ሙክታር ሮቦው የሶማሊያ የሀይማኖት ጉዳዮች ሚኒስትር ሆነው ተሹመዋል።

በሌላ በኩል ፤ የቀድሞው የአልሸባብ ሰው በካቢኔ ውስጥ መካተታቸው አሜሪካን እንዳላስደሰታት በአንድንድ የሶማሊያ መገናኛ ብዙሃን ቢነገርም አሜሪካ በካቢኔው ደስተኛ እንደሆነች በመግለፅ ለፕሬዜዳንት ሼክ ሀሰን ሙሀሙድና ጠ/ሚ ሀምዛ አብዲ ባሬ " እንኳን ደስ አላችሁ " ስትል ሶማሊያ በሚገኘው ኤምባሲ በኩል መልዕክቷን አስተላልፋለች።

አሜሪካ ፤ ለሶማሊያ የምታደርገውን ድጋፎች አጠናክራ እንደምትቀጥልበትም ገልፃለች።

ሀገሪቱ በሶማሊያ የሚኒቀሳቀሰው " አልሸባብ "ን ለመዋጋት ሰፊ እንቅስቃሴ ከሚያደርጉ ሀገራት በቀዳሚነት ስሟ የሚነሳ ሲሆን በኢኮኖሚያዊና ሰብዓዊ ድጋፍ በኩልም በሚሊዮን ዶላሮችን ለሶማሊያ ድጋፍ ታደርጋለች።

@tikvahethiopia
#መግለጫ

ከግዜ ወደ ግዜ እየጨመረ በሚገኘው የአካል ጉዳተኞች ጠቅላላ የመብቶች ጥሰት በተመለከተ የኢትዮጵያ የሕግ ባለሞያ አካል ጉዳተኞች ማህበር ጋዜጣዊ መግለጫ አውጥቷል።

ማህበሩ በላከልን መግለጫ ፥ የተደራሽነት መብትን ጨምሮ የትምህርት፣ የጤና፣ የስራ እና የቅጥር መብቶች እና ሌሎች የአካል ጉዳተኞች መብቶች በየግዜው እየተጣሱ እና ለጥሰቶቹ ሀላፊነት የሚወስድ አካል ሳይኖር እንዲሁም ጥፋተኞችም ተጠያቂ ሳይደረጉ የመብት ጥሰቶቹ ተድበስብሰው በመታለፍ ላይ ናቸው ብሏል።

የአካል ጉዳተኞችን የመብት ጥሰቶችን ተከትሎ ተጠያቂነት ባለመኖሩም ጥሰት የሚፈጸምባቸው ሰዎች ሳይካሱ እየቀሩ እና ጥሰት ፈጻሚዎችም ድርጊታቸውን ትክክል አድርገው እንዲወስዱትና የመብት ጥሰቱም ያለከልካይ እንዲቀጥል ምክንያት ሆኗል ብሏል።

አሁን በተግባር እንደሚታየው የአካል ጉዳተኞች የመብት ጉዳዮች በግለሰቦች መዳፍ ላይ የተንጠለጠሉ በመሆናቸው፤ አካል ጉዳተኛው ማህበረሰብ መብቱን እንደምጽዋት እንዲጠይቅና እንዲቀበል ተገዷል ሲልም ገልጿል።

ማህበሩ ፥ በአካልጉዳተኛ ግለሰቦች ላይ ከሚፈጸሙ አይነተብዙ የመብት ጥሰቶች በተጨማሪ ከመንግስት በኩል አካል ጉዳተኞችን በቁልፍ ሀገራዊ ጉዳዮች ላይ ከአካታችነት መሻት በሚመነጭ ተነሳሽነት የማካተት ስራዎች በበቂ ሁኔታ እየተሰሩ አይደለም ብሏል።

ከሀገሪቱ ህዝብ ቁጥር ከ17.6 በላይ የሚሸፍነው አካል ጉዳተኛው ማህበረሰብ እንደሆነ ያታወቃል ያለው ማህበሩ የተለየ በጀት የማይበጀትለት መሆኑና የመብት ጥያቄ በሚያነሳበት ግዜም ፖለቲካዊ ውክልና የሌለው ማህበረሰብ መሆኑን ተከትሎ ምላሽ ሳይሰጠው በመቅረት ላይ ነው ብሏል።

ማህበሩ እየተባባሰ መጥቷል ላለቸው የመብቶች ጥሰት መፍትሄ ያለውን በዝርዝር አስቀመጧል።

(ሙሉ መግለጫው ከላይ ተያይዟል)

@tikvahethiopia