#AAU
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ግጭት ካለባቸው አካባቢዎች የመጡና የተመረቁ ተማሪዎቹ በታኅሳስ መጨረሻ ግቢውን ለቀው እንዲወጡ አሳሰበ፡፡
እነዚህ 41 የዩኒቨርሲቲው የቀድሞ ተማሪዎች፣ ከኦሮሚያ ክልል ወለጋ አካባቢ፣ ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን እና ከትግራይ ክልል የመጡ ሲሆኑ፣ የመጡበት አካባቢ የፀጥታ ችግር በመኖሩ ከተመረቁ በኋላም በዩኒቨርሲቲው ለመቆየት ማመልከቻ አስገብተው ነበር፡፡
ተማሪዎቹ ከተመረቁ በኋላ በግቢው ውስጥ ሆነው የመኝታና የምግብ አገልግሎት ሲያገኙ መቆየታቸውን የዩኒቨርሲቲው የአስተዳደርና የተማሪዎች አገልግሎት ም/ፕሬዝዳንት ማቲዮስ ኤርሳሞ (ዶ/ር) ገልጸዋል፡፡
አሁን ላይ ግን ተማሪዎቹ ግቢውን ለቀው እንዲወጡ ማሳሰቢያ መስጠቱን ተናግረዋል፡፡
አንዳንድ ተመራቂዎቹ አዲስ አበባ ውስጥ ሥራ ካገኙ በኋላም በግቢው መኖር ቀጥለዋል ያሉት ምክትል ፕሬዝዳንቱ፤ ተማሪዎቹ የመጡበት አካባቢ በትክክል የፀጥታ ስጋት ያለበት ስለመሆኑ ማረጋገጥ አለመቻሉን ገልጸዋል።
ከትግራይ ክልል የመጡት ተመራቂዎች በጊዜ ሂደት ሥራ በማግኘታቸውና ወደ መኖሪያቸው በመመለሳቸው አሁን ላይ በዩኒቨርሲቲው ውስጥ ያሉ ከትግራይ የመጡ ተማሪዎች ቁጥር 'ጥቂት' መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
''ተማሪዎች ከተመረቁ በኋላ ከዩኒቨርሲቲው ጋር ያላቸው ሕጋዊ ውል ይቋረጣል'' ያሉት ኃላፊው፤ ዩኒቨርሲቲው ለተመረቁ ተማሪዎች ወጪ የማውጣት ሥልጣን እንደሌለው ገልጸዋል፡፡
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎቹን መስከረም 30/2014 ዓ.ም ማስመረቁ ይታወሳል።
ምንጭ፦ ሪፖርተር ጋዜጣ
@tikvahuniversity
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ግጭት ካለባቸው አካባቢዎች የመጡና የተመረቁ ተማሪዎቹ በታኅሳስ መጨረሻ ግቢውን ለቀው እንዲወጡ አሳሰበ፡፡
እነዚህ 41 የዩኒቨርሲቲው የቀድሞ ተማሪዎች፣ ከኦሮሚያ ክልል ወለጋ አካባቢ፣ ከቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መተከል ዞን እና ከትግራይ ክልል የመጡ ሲሆኑ፣ የመጡበት አካባቢ የፀጥታ ችግር በመኖሩ ከተመረቁ በኋላም በዩኒቨርሲቲው ለመቆየት ማመልከቻ አስገብተው ነበር፡፡
ተማሪዎቹ ከተመረቁ በኋላ በግቢው ውስጥ ሆነው የመኝታና የምግብ አገልግሎት ሲያገኙ መቆየታቸውን የዩኒቨርሲቲው የአስተዳደርና የተማሪዎች አገልግሎት ም/ፕሬዝዳንት ማቲዮስ ኤርሳሞ (ዶ/ር) ገልጸዋል፡፡
አሁን ላይ ግን ተማሪዎቹ ግቢውን ለቀው እንዲወጡ ማሳሰቢያ መስጠቱን ተናግረዋል፡፡
አንዳንድ ተመራቂዎቹ አዲስ አበባ ውስጥ ሥራ ካገኙ በኋላም በግቢው መኖር ቀጥለዋል ያሉት ምክትል ፕሬዝዳንቱ፤ ተማሪዎቹ የመጡበት አካባቢ በትክክል የፀጥታ ስጋት ያለበት ስለመሆኑ ማረጋገጥ አለመቻሉን ገልጸዋል።
ከትግራይ ክልል የመጡት ተመራቂዎች በጊዜ ሂደት ሥራ በማግኘታቸውና ወደ መኖሪያቸው በመመለሳቸው አሁን ላይ በዩኒቨርሲቲው ውስጥ ያሉ ከትግራይ የመጡ ተማሪዎች ቁጥር 'ጥቂት' መሆኑን ጠቁመዋል፡፡
''ተማሪዎች ከተመረቁ በኋላ ከዩኒቨርሲቲው ጋር ያላቸው ሕጋዊ ውል ይቋረጣል'' ያሉት ኃላፊው፤ ዩኒቨርሲቲው ለተመረቁ ተማሪዎች ወጪ የማውጣት ሥልጣን እንደሌለው ገልጸዋል፡፡
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎቹን መስከረም 30/2014 ዓ.ም ማስመረቁ ይታወሳል።
ምንጭ፦ ሪፖርተር ጋዜጣ
@tikvahuniversity
👍297👎117😁20🎉11❤9🤩4😱2😢2🔥1
#AAU
" ... የዩኒቨርሲቲው ተማሪ ያልሆኑ ግለሰቦች በግቢው ረብሻ ለመቀስቀስ ሞክረዋል። በአሁኑ ሰዓት አንድም የታሰረ ተማሪ የለም " - የአ.አ.ዩ የፕሬዝዳንት ጽ/ቤት አማካሪ
@tikvahuniversity በአዲሰ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትላንትና እሁድ ስለተከሰተው ነገር የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ጽ/ቤት የኮሚዩኒኬሽን አማካሪ ኢንጂነር ውባየሁ ማሞን ጠይቋል።
ኢጂነር ውባየሁ ማሞ ፦ " ላለፉት ስድስት ቀናት የተለያዩ ነገሮች በግቢው አስተውለናል። ከተማሪዎቻችን ጋር ስንወያይ ቆይተናል። በመጨረሻ ከተማሪዎች አጀንዳ ውጪ የሆነ ነገር እንዳለ ስናውቅ እርምጃ ወስደናል " ብለዋል።
አማካሪው ፤ " ትላንት የዩኒቨርሲቲው ተማሪ ያልሆኑ አልፈው ገብተው ረብሻ ለመቀስቀስ የሞከሩ ስምንት ግለሰቦች ተይዘው በሕግ ክትትል ስር ይገኛሉ " ሲሉም ገልፀዋል።
" ግለሰቦቹ የፖለቲካ አጀንዳ ይኖራቸዋል። " ያሉት ኢ/ር ውባየሁ " ንጹሀን ተማሪዎች ላይ ያልተገባ ነገር ለመፈጸም እንደገቡ ስላወቅን ግለሰቦቹን ለይተን ይዘናል " ሲሉ አስረድተውናል።
" በአሁኑ ሰዓት አንድም የታሰረ ተማሪ የለም። አንድም ከትምህርት ገበታው ያቋረጠ ተማሪ የለም። የመማር ማስተማር ሂደቱ ሙሉ በሙሉ እየሄደ ነው " ሲሉም ተናግረዋል።
ኢ/ር ውባየሁ ፥ " በተለያዩ ማህበራዊ መገናኛ ብዙሃን እየተወራ ያለው ሀሰት ነው። ትክክለኛ መረጃ እየወጣ አይደለም። ተማሪዎችንና ቤተሰብን የሚረብሽ ነገር ነው እየወጣ ያለው። " ብለዋል።
አማካሪው ፤ ትላንትና ግለሰቦቹ ለማምለጥ ሲሞክሩ ለመያዝ የተሰራ ነገር ነበር ያሉ ሲሆን በዚህም ምክንያት የተፈጠረው ችግር ወዲያው ከመንግስት አካላት ጋር በመሆን ተፈቷል ሲሉ ገልፀዋል።
@tikvahethiopia
" ... የዩኒቨርሲቲው ተማሪ ያልሆኑ ግለሰቦች በግቢው ረብሻ ለመቀስቀስ ሞክረዋል። በአሁኑ ሰዓት አንድም የታሰረ ተማሪ የለም " - የአ.አ.ዩ የፕሬዝዳንት ጽ/ቤት አማካሪ
@tikvahuniversity በአዲሰ አበባ ዩኒቨርሲቲ ትላንትና እሁድ ስለተከሰተው ነገር የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ጽ/ቤት የኮሚዩኒኬሽን አማካሪ ኢንጂነር ውባየሁ ማሞን ጠይቋል።
ኢጂነር ውባየሁ ማሞ ፦ " ላለፉት ስድስት ቀናት የተለያዩ ነገሮች በግቢው አስተውለናል። ከተማሪዎቻችን ጋር ስንወያይ ቆይተናል። በመጨረሻ ከተማሪዎች አጀንዳ ውጪ የሆነ ነገር እንዳለ ስናውቅ እርምጃ ወስደናል " ብለዋል።
አማካሪው ፤ " ትላንት የዩኒቨርሲቲው ተማሪ ያልሆኑ አልፈው ገብተው ረብሻ ለመቀስቀስ የሞከሩ ስምንት ግለሰቦች ተይዘው በሕግ ክትትል ስር ይገኛሉ " ሲሉም ገልፀዋል።
" ግለሰቦቹ የፖለቲካ አጀንዳ ይኖራቸዋል። " ያሉት ኢ/ር ውባየሁ " ንጹሀን ተማሪዎች ላይ ያልተገባ ነገር ለመፈጸም እንደገቡ ስላወቅን ግለሰቦቹን ለይተን ይዘናል " ሲሉ አስረድተውናል።
" በአሁኑ ሰዓት አንድም የታሰረ ተማሪ የለም። አንድም ከትምህርት ገበታው ያቋረጠ ተማሪ የለም። የመማር ማስተማር ሂደቱ ሙሉ በሙሉ እየሄደ ነው " ሲሉም ተናግረዋል።
ኢ/ር ውባየሁ ፥ " በተለያዩ ማህበራዊ መገናኛ ብዙሃን እየተወራ ያለው ሀሰት ነው። ትክክለኛ መረጃ እየወጣ አይደለም። ተማሪዎችንና ቤተሰብን የሚረብሽ ነገር ነው እየወጣ ያለው። " ብለዋል።
አማካሪው ፤ ትላንትና ግለሰቦቹ ለማምለጥ ሲሞክሩ ለመያዝ የተሰራ ነገር ነበር ያሉ ሲሆን በዚህም ምክንያት የተፈጠረው ችግር ወዲያው ከመንግስት አካላት ጋር በመሆን ተፈቷል ሲሉ ገልፀዋል።
@tikvahethiopia
👍1.64K👎494😢66🥰43❤27😱27👏23
#Huawei #AAU
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲና ሁዋዌ ሃንድሼኪንግ ፎረም በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ትናንት ተከፍቷል።
አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ያዘጋጀው የምርምርና ፌር ሳምንት Research and Fairs Week በትናትናው ዕለት ተጀምሯል።
በዚህ። የተለያዩ ኤግዚቢሽኖች ተከፍተው ፤ በአዲስ ዩኒቨርስቲ በምርምር ዘርፍ የተሰሩ የምርምር ስራዎች ለእይታ ቀርበው ተጎብኝተዋል።
በዓለም አቀፍ ደረጃ በአይሲቲ መሰረተልማት እና ስማርት መጠቀሚያዎችን በማምረት ቀዳሚ የሆነው ሁዋዌ በዩኒቨርስቲው በመገኘት የ Handshaking Forum ጆብ ፌር ከፍቷል ፥ ይህ ዛሬ የሚጠናቀቅ ይሆናል።
ሁዋዌ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ጋር በመተባበር Handshaking Forum በሚል የተመራቂ ተማሪዎችን ሲቪ ሲያሰባስብ ለ2ኛ ጊዜው ሲሆን በዚህ ፎረም አቅም ያላቸው ተመራቂ ተማሪዎችን ከአሰሪዎች ጋር ለማገናኘት ይሰራል።
ከሁዋዌ ባገኘነው መረጃ መሰረት ሁዋዌ አዲስ ለተመረቁ ምሩቃን ያዘጋጀው የኢንተርንሺፕ ፕሮግራም ሲኖረው በዚህም ለ3 ወራት በሁዋዌ ኢትዮጵያ ቢሮ እንዲሰለጥኑ ካደረገ በኃላ የተሻለ አፈጻጸም ያሰስመዘገቡትን ይቀጥራል።
ባለፈው ዓመት ለ250 ተማሪዎች የኢንተርንሺፕ እድል የፈጠረ ሲሆን ከነዚያም መካከል 200 ያህሉ በድርጅቱ ተቀጥረዋል። በዚህ ዓመት 300 ያህል የመቀበል እቅድ ሲኖረው እስካሁን ከ90 በላይ ተቀብሏል።
@tikvahethiopia
የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲና ሁዋዌ ሃንድሼኪንግ ፎረም በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ትናንት ተከፍቷል።
አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ያዘጋጀው የምርምርና ፌር ሳምንት Research and Fairs Week በትናትናው ዕለት ተጀምሯል።
በዚህ። የተለያዩ ኤግዚቢሽኖች ተከፍተው ፤ በአዲስ ዩኒቨርስቲ በምርምር ዘርፍ የተሰሩ የምርምር ስራዎች ለእይታ ቀርበው ተጎብኝተዋል።
በዓለም አቀፍ ደረጃ በአይሲቲ መሰረተልማት እና ስማርት መጠቀሚያዎችን በማምረት ቀዳሚ የሆነው ሁዋዌ በዩኒቨርስቲው በመገኘት የ Handshaking Forum ጆብ ፌር ከፍቷል ፥ ይህ ዛሬ የሚጠናቀቅ ይሆናል።
ሁዋዌ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ጋር በመተባበር Handshaking Forum በሚል የተመራቂ ተማሪዎችን ሲቪ ሲያሰባስብ ለ2ኛ ጊዜው ሲሆን በዚህ ፎረም አቅም ያላቸው ተመራቂ ተማሪዎችን ከአሰሪዎች ጋር ለማገናኘት ይሰራል።
ከሁዋዌ ባገኘነው መረጃ መሰረት ሁዋዌ አዲስ ለተመረቁ ምሩቃን ያዘጋጀው የኢንተርንሺፕ ፕሮግራም ሲኖረው በዚህም ለ3 ወራት በሁዋዌ ኢትዮጵያ ቢሮ እንዲሰለጥኑ ካደረገ በኃላ የተሻለ አፈጻጸም ያሰስመዘገቡትን ይቀጥራል።
ባለፈው ዓመት ለ250 ተማሪዎች የኢንተርንሺፕ እድል የፈጠረ ሲሆን ከነዚያም መካከል 200 ያህሉ በድርጅቱ ተቀጥረዋል። በዚህ ዓመት 300 ያህል የመቀበል እቅድ ሲኖረው እስካሁን ከ90 በላይ ተቀብሏል።
@tikvahethiopia
👍1