TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.7K photos
1.6K videos
216 files
4.35K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ጥቆማ አድርሱ~~8482👆

ህብረተሰቡ የተሰቀሉ የአልኮል ማስታወቂያ ቢልቦርዶች ሲመለከት #በ8482 በመደወል ጥቆማ እንዲሰጥ ተጠየቀ። በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የወጣው አዋጅ ቁጥር 1112/2011 የአልኮል ምርት በማንኛውም በብሮድካስትና ቢል ቦርድ ማስተዋወቅ የተከለከሉ ድንጋጌዎች መውጣቱን ተከትሎ አብዛኛው የአልኮል ምርት አምራቾች ህጉን ተከትሎ በአ/አ ስታዲየም ዙሪያና በተለያዩ ቦታዎች የተሰቀሉ ቢልቦርዶችን #በማንሳት ላይ ላይ መሆናቸውን የኢትዮጵያ የምግብና መድኃኒት ቁጥጥር ባለስልጣን አስታውቋል። ሆኖም በአንዳንድ ቦታዎች እስካሁን ድረስ የቢልቦርድ ማስታወቂያ ያልተነሱ መሆኑንና የአልኮል አምራች ድርጅትና የማስታወቂያ ሰሪ ድርጅቶች በየቦታው የተሰቀለውን ቢልቦርድ እንዲያነሱ አሳስቦ ህብረተሰቡም በየቦታው የተሰቀሉ ቢልቦርዶች ሲመለከት በ8482 በመደወል #ጥቆማ እንዲሰጥ ጠይቋል።

√√በህዝብ ተወካዬች ም/ቤት በቅርቡ በፀደቀውን የምግብና መድኃኒት አስተዳደር አዋጅ 1112 መሰረት ከዛሬ ግንቦት 21 ጀምሮ የአልኮል ማስታወቂያዎችን በብሮድካስት ማስተዋወቅ የሚከለክለው ህግ ተግባራዊ እንደሚያደርግ መግለፁ ይታወሳል ።

Via waltainfo.com
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#8482

የተሰቀሉ የአልኮል ማስታወቂያ ቢልቦርዶች ስትመለከቱ #በ8482 በመደወል ጥቆማ እንድትሰጡ ተጠይቃችኃል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia