TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.4K photos
1.51K videos
215 files
4.12K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የዕርቅ ሃሳብ አለኝ!

ቲክቫህ ኢትዮጵያ (Tikvah-Ethiopia) ትላንት ከዕርቀ ሰላም ኮሚሽን ጋር በመተባበር በይፋ ያስጀመርነው ንቅናቄ ወጣቶች ከያሉበት ሆነው በአከባቢያቸው ስላለ የዕርቅ ሥርዓት ጥናት በማድረግና በመጠየቅ ከ5-10 ገጽ በሚሆን አጭር የገለጻ ጹሑፍ ውድድር ነው፡፡

በውድድሩ የሚሳተፉ ወጣቶች በቅድሚያ የሚመዘገቡ ሲሆን ከ15-20 ቀናት የመዘጋጃ ጊዜ ይሰጣቸዋል፡፡ ተወዳዳሪዎች ፅሁፋቸውን የሚያቀርቡት #በመረጡት ሀገራዊ ቋንቋ ነው።

በሚያስገቡት ጹሑፍ ስለ አከባቢያቸው አጠቃላይ ገለጻ፣ ማስተዋወቅ ስለሚፈልጉት ባህላዊ የእርቅ ሥርዓት ሥርዓቱ በአሁኑ ወቅት በማህበረሰቡ ዘንድ ያለውን ተቀባይነት በተጨማሪም በሥራው ወቅት የተገነዘቡት እና የታዘቡትን ምልከታ ማካተት የሚጠበቅባቸው ይሆናል፡፡

በመቀጠልም ያስገቡት #ጹሑፍ 'የኢትዮጵያ ዕርቀ ሰላም ኮሚሽን' በሚያዋቅረው ቡድን #ከተገመገመ በኃላ የጹሑፋቸው ይዘት እና አቀራረባቸው በተለያዩ የማወዳደሪያ መስፈርቶች ከተገመገመ በኃላ አሸናፊዎች የሚለዩ ይሆናል፡፡

ከዚህም በተጨማሪ በውድድሩ የሚሳተፉ እንዲሁም ዋና ዋና መስፈርቶችን ያሟሉ ተሳታፊዎች በሙሉ ሰርተፍኬት ይዘጋጅላቸዋል ፤ #ለአሸናፊዎች ደግሞ 'ልዩ ሽልማት' የሚበረከት ይሆናል።

የምዝገባ ሂደቶችን በቅርቡ የምናሳውቅ ይሆናል!

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia