#AddisAbeba #Lyon
ኢ/ር ታከለ ኡማ ከፈረንሳይዋ ሊዩን ከተማ ፕሬዝዳንት ዴቪድ ኬሚልፊልድ ጋር የትብብር ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቱ በአዲስ አበባ እና በሊዬን ከተማ መካከል ያለውን ግንኙነት ይበልጥ የሚያጠናክር ሲሆን በተለያዩ መስኮችም በጋራ ለመስራት የሚያስችል ነው።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ኢ/ር ታከለ ኡማ ከፈረንሳይዋ ሊዩን ከተማ ፕሬዝዳንት ዴቪድ ኬሚልፊልድ ጋር የትብብር ስምምነት ተፈራርመዋል። ስምምነቱ በአዲስ አበባ እና በሊዬን ከተማ መካከል ያለውን ግንኙነት ይበልጥ የሚያጠናክር ሲሆን በተለያዩ መስኮችም በጋራ ለመስራት የሚያስችል ነው።
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#INSA
የዛሬው የኢንተርኔት መቋረጥ ምክንያት...
በሀገሪቱ የፋይናስ ተቋሞች ላይ ሊደርስ የነበረ የሳይበር ጥቃትን ለመከላከል በዛሬው ዕለት INSA ኔትዎርክ ለማቋረጥ ተገድዶ እንደነበረ የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈፃኒ ወ/ሪት ፍሬህይወት ታምሩ ገለፁ። ዛሬ የተከሰተው የኢንተርኔት መቋረጥ በኢትዮ ቴሌኮም ቁጥጥር ስር የነበረ እንዳልሆነና፤ ታቅዶም እንዳልነበር አስታውቀዋል።
ዋና ስራ አስፈፃሚዋ ጉዳዩ ጊዜ የሚሰጥ አልነበረም፤እኛም መቋረጡን ለደንበኞቻችን ለመንገር ግዜ አልነበረንም፣ ለጥቂት ደቂቃ በማቋረጥ ጥቃቱን ለመከላከል ይቻላል ተብሎ የተወሰደ እርምጃ ነበር ብለዋል።
ከINSA ጋር እየተነጋገርን ነው የምንሰራው ያሉት ወ/ሪት ፍሬህይወት በዛሬው ዕለት ግን ከቁጥጥር ውጭ የሆነ ችግር አጋጥሟቸው የነበር ይመስለኛል፤ አሁን በጉዳዩ ላይ እየተነጋገርን ነው ብለዋል። ለኢንተርኔት መቋረጡ ይቅርታ ጠይቀዋል።
(ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት)
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
የዛሬው የኢንተርኔት መቋረጥ ምክንያት...
በሀገሪቱ የፋይናስ ተቋሞች ላይ ሊደርስ የነበረ የሳይበር ጥቃትን ለመከላከል በዛሬው ዕለት INSA ኔትዎርክ ለማቋረጥ ተገድዶ እንደነበረ የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈፃኒ ወ/ሪት ፍሬህይወት ታምሩ ገለፁ። ዛሬ የተከሰተው የኢንተርኔት መቋረጥ በኢትዮ ቴሌኮም ቁጥጥር ስር የነበረ እንዳልሆነና፤ ታቅዶም እንዳልነበር አስታውቀዋል።
ዋና ስራ አስፈፃሚዋ ጉዳዩ ጊዜ የሚሰጥ አልነበረም፤እኛም መቋረጡን ለደንበኞቻችን ለመንገር ግዜ አልነበረንም፣ ለጥቂት ደቂቃ በማቋረጥ ጥቃቱን ለመከላከል ይቻላል ተብሎ የተወሰደ እርምጃ ነበር ብለዋል።
ከINSA ጋር እየተነጋገርን ነው የምንሰራው ያሉት ወ/ሪት ፍሬህይወት በዛሬው ዕለት ግን ከቁጥጥር ውጭ የሆነ ችግር አጋጥሟቸው የነበር ይመስለኛል፤ አሁን በጉዳዩ ላይ እየተነጋገርን ነው ብለዋል። ለኢንተርኔት መቋረጡ ይቅርታ ጠይቀዋል።
(ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት)
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
#INSA
በፋይናንስ ተቋማት ላይ ሊደርስ የነበረውን የሳይበር ጥቃት ማክሸፍ ተቻለ!
ዛሬ በፋይናንስ ተቋማት ላይ ሊደርስ የነበረውን የሳይበር ጥቃት ሙሉ በሙሉ ማክሸፍ መቻሉን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ አስታወቀ፡፡
የፋይናንስ ተቋሞችን የሳይበር ጥቃትን ለመከላከል የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ ኔትወርኩን ከ15 እስከ 20 ደቂቃዎች ለማቋረጥ ተገድዶ እንደነበር የኤጀንሲው ምክትል ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር ወርቁ ጋቸና ተናግረዋል፡፡
ተመሳሳይ ችግሮችን ለማክሸፍ ኤጀንሲው ከኢትዮ ቴልኮም ጋር በመሆን እየሰራ መሆኑንም ምክትል ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል፡፡
በኤጀንሲ ውስጥ ኢትዮ ሰርት የሚባል የፋይናንስ ተቋማትን ለ24 ሰዓት የሚከታተል እና አዲስ ጥቃቶች ሲቃጡ የመከላከል ተግባር ያለው ክፍል መኖሩን ገልጸዋል፡፡ በዚሁ ክፍል ጥቃቱ ሳይደርስ መከላከል መቻሉን ኢንጅነር ወርቁ ተናግረዋል፡፡
ስራው ብዙ ጊዜ የተለመደውና የኔትወርክ ለውጥ የሚደረገው ብዙ ሰው ኢንተርኔት በማይጠቀምበት ሰአት ምሽት እንደነበር የተገለጸ ሲሆን ዛሬ ላይ የተፈጠረው አስቸኳይ ስለነበር ቀን ላይ እርምጃው መወሰዱን ተጠቁሟል፡፡ ጥቃቱ ከየት እንደተሰነዘረ ዝርዝር ጉዳዮችን እየተመለከቱ እንደሆነም ገልጸዋል፡፡
(ኢቢሲ)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በፋይናንስ ተቋማት ላይ ሊደርስ የነበረውን የሳይበር ጥቃት ማክሸፍ ተቻለ!
ዛሬ በፋይናንስ ተቋማት ላይ ሊደርስ የነበረውን የሳይበር ጥቃት ሙሉ በሙሉ ማክሸፍ መቻሉን የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ አስታወቀ፡፡
የፋይናንስ ተቋሞችን የሳይበር ጥቃትን ለመከላከል የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ ኔትወርኩን ከ15 እስከ 20 ደቂቃዎች ለማቋረጥ ተገድዶ እንደነበር የኤጀንሲው ምክትል ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር ወርቁ ጋቸና ተናግረዋል፡፡
ተመሳሳይ ችግሮችን ለማክሸፍ ኤጀንሲው ከኢትዮ ቴልኮም ጋር በመሆን እየሰራ መሆኑንም ምክትል ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል፡፡
በኤጀንሲ ውስጥ ኢትዮ ሰርት የሚባል የፋይናንስ ተቋማትን ለ24 ሰዓት የሚከታተል እና አዲስ ጥቃቶች ሲቃጡ የመከላከል ተግባር ያለው ክፍል መኖሩን ገልጸዋል፡፡ በዚሁ ክፍል ጥቃቱ ሳይደርስ መከላከል መቻሉን ኢንጅነር ወርቁ ተናግረዋል፡፡
ስራው ብዙ ጊዜ የተለመደውና የኔትወርክ ለውጥ የሚደረገው ብዙ ሰው ኢንተርኔት በማይጠቀምበት ሰአት ምሽት እንደነበር የተገለጸ ሲሆን ዛሬ ላይ የተፈጠረው አስቸኳይ ስለነበር ቀን ላይ እርምጃው መወሰዱን ተጠቁሟል፡፡ ጥቃቱ ከየት እንደተሰነዘረ ዝርዝር ጉዳዮችን እየተመለከቱ እንደሆነም ገልጸዋል፡፡
(ኢቢሲ)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ተጠርጣሪዎችን ለመያዝ የተሰማሩ ሁለት ፖሊሶች ተገደሉ!
በምስራቅ ሸዋ ዞን አዳማ ወረዳ አዱላላ ቦኩ በሚባል ቀበሌ በፍርድ ቤት ትዕዛዝ ተጠርጣሪን ለመያዝ የተሰማሩ ሁለት የዞኑ የፖሊስ አባላት መገደላቸውን ፖሊስ አስታወቀ።
የምስራቅ ሸዋ ዞን ፖሊስ አዛዥ የሆኑት ኮማንደር ሽፈራው ጉቱ "ፖሊሶች ወደ ቀበሌው ሄደው ተጠርጣሪዎቹን በቁጥጥር ሥር ለማዋል ሲሉ 'ለምን ይያዛሉ?' በሚል ረብሻ ተነስቶ የአከባቢው ሰዎች በፖሊስ አባሎቻችን ላይ ጉዳት አደረሱ" ሲሉ ለቢቢሲ ተናግረዋል።
በአካባቢው ነዋሪዎች የተቃጣው ጥቃት የሁለት የፖሊስ አባላቶችን ህይወት ከመቅጠፉም በላይ አንድ ሲቪል ህይወቱ ያለፈ ሲሆን በሁለት የፖሊስ አባላት ላይ ደግሞ ጉዳት ማድረሱን ኮማንደር ሽፈራው ተናግረዋል።
ረቡዕ ጠዋት አንድ ሰዓት ገደማ ላይ በተፈጠረው ክስተት ጉዳት የደረሰባቸው ሁለቱ የፖሊስ አባላት ሆስፒታል ተኝተው የህክምና ክትትል እየተደረገላቸው መሆኑም ታውቋል።
የተፈጠረው ምን ነበር?
ረቡዕ ጠዋት የምስራቅ ሸዋ ዞን ፖሊስ አባላት ሃሰተኛ መስክርነት በመስጠት የተጠረጠሩ ሶስት ግለሰቦችን በፍርድ ቤት ትዕዛዝ መሰረት በቁጥጥር ሥር ለማዋል ወደ አዱላላ ቦኩ ቀበሌ ያመራሉ።
"ከዚህ በፊት ሶስቱ ግለሰቦቹ 'ሰው ገድሏል' በማለት በሃሰት መሰከሩ። የክስ መዝገቡ ምረመራ ከተጠናቀቀ በኋላ በድጋሚ ቃላቸውን እንዲሰጡ ሲጠየቁ ፍቃደኛ ሳይሆኑ ቀሩ። የሰጡት ምስክርነት የሃሰት መሆኑ ሲታወቅ ፍርድ ቤት ተይዘው እንዲቀርቡ ትዕዛዝ ሰጠ። የፍርድ ቤቱን ትዕዛዝ ለመፈጸም ፖሊሶች ወደ ስፍራው ከተሰማሩ በኋላ ነው ይህ የሆነው" በማለት የዞኑ ፖሊስ አዛዥ ያስረዳሉ።
More👇
https://telegra.ph/BBC-12-05
(BBC አማርኛው አገልግሎት)
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
በምስራቅ ሸዋ ዞን አዳማ ወረዳ አዱላላ ቦኩ በሚባል ቀበሌ በፍርድ ቤት ትዕዛዝ ተጠርጣሪን ለመያዝ የተሰማሩ ሁለት የዞኑ የፖሊስ አባላት መገደላቸውን ፖሊስ አስታወቀ።
የምስራቅ ሸዋ ዞን ፖሊስ አዛዥ የሆኑት ኮማንደር ሽፈራው ጉቱ "ፖሊሶች ወደ ቀበሌው ሄደው ተጠርጣሪዎቹን በቁጥጥር ሥር ለማዋል ሲሉ 'ለምን ይያዛሉ?' በሚል ረብሻ ተነስቶ የአከባቢው ሰዎች በፖሊስ አባሎቻችን ላይ ጉዳት አደረሱ" ሲሉ ለቢቢሲ ተናግረዋል።
በአካባቢው ነዋሪዎች የተቃጣው ጥቃት የሁለት የፖሊስ አባላቶችን ህይወት ከመቅጠፉም በላይ አንድ ሲቪል ህይወቱ ያለፈ ሲሆን በሁለት የፖሊስ አባላት ላይ ደግሞ ጉዳት ማድረሱን ኮማንደር ሽፈራው ተናግረዋል።
ረቡዕ ጠዋት አንድ ሰዓት ገደማ ላይ በተፈጠረው ክስተት ጉዳት የደረሰባቸው ሁለቱ የፖሊስ አባላት ሆስፒታል ተኝተው የህክምና ክትትል እየተደረገላቸው መሆኑም ታውቋል።
የተፈጠረው ምን ነበር?
ረቡዕ ጠዋት የምስራቅ ሸዋ ዞን ፖሊስ አባላት ሃሰተኛ መስክርነት በመስጠት የተጠረጠሩ ሶስት ግለሰቦችን በፍርድ ቤት ትዕዛዝ መሰረት በቁጥጥር ሥር ለማዋል ወደ አዱላላ ቦኩ ቀበሌ ያመራሉ።
"ከዚህ በፊት ሶስቱ ግለሰቦቹ 'ሰው ገድሏል' በማለት በሃሰት መሰከሩ። የክስ መዝገቡ ምረመራ ከተጠናቀቀ በኋላ በድጋሚ ቃላቸውን እንዲሰጡ ሲጠየቁ ፍቃደኛ ሳይሆኑ ቀሩ። የሰጡት ምስክርነት የሃሰት መሆኑ ሲታወቅ ፍርድ ቤት ተይዘው እንዲቀርቡ ትዕዛዝ ሰጠ። የፍርድ ቤቱን ትዕዛዝ ለመፈጸም ፖሊሶች ወደ ስፍራው ከተሰማሩ በኋላ ነው ይህ የሆነው" በማለት የዞኑ ፖሊስ አዛዥ ያስረዳሉ።
More👇
https://telegra.ph/BBC-12-05
(BBC አማርኛው አገልግሎት)
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
#NobelPeacePrize #DrAbiyAhemed
"ጠ/ሚር አብይ የኖርዌይ እና የአለም አቀፍ ሚድያ ጋዜጠኞችን ቢያገኙ ምኞቴ ነበር"--- የኖቤል ኢንስቲትዩት ዳይሬክተር
"የኖቤል ሽልማት ፕሮግራም ረዥም/ሰፋ ያለ ነው። ለአንድ የሀገር መሪ ሁሉም ፕሮግራሞች ላይ መካፈል አስቸጋሪ ነው፣ በተለይ ሀገር ውስጥ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች ባሉበት ወቅት"--- የጠ/ሚሩ ፕረስ ሰክረታሪ ቢለኔ ስዩም
የኖርዌይ የኖቤል ኢንስቲትዩት ዳይሬክተር ኦላቭ ጆልስታድ ጠ/ሚር አብይ ከአምስት ቀን በሁዋላ ሽልማታቸውን በሚቀበሉበት ወቅት ጥያቄዎች የሚጠየቁበት ፕሮግራም ላይ እንደማይገኙ ገልፀው "ይህ በጣም ችግር ነው። ጠ/ሚር አብይ የኖርዌይ እና የአለም አቀፍ ሚድያ ጋዜጠኞችን ቢያገኙ ምኞቴ ነበር" ብለው ለአሶሼትድ ፕረስ ተናግረዋል።
ዛሬ የጠ/ሚሩ ፕረስ ሰክረታሪ ቢለኔ ስዩም ለAssociated Press ጋዜጠኛው ኤልያስ መሰረት በሰጡት መረጃ - "የኖቤል ሽልማት ፕሮግራም ረዥም/ሰፋ ያለ ነው። ለአንድ የሀገር መሪ ሁሉም ፕሮግራሞች ላይ መካፈል አስቸጋሪ ነው፣ በተለይ ሀገር ውስጥ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች ባሉበት ወቅት። ስለዚህ ጠ/ሚሩ በተመረጡ እና ቅድሚያ በሚሰጣቸው ፕሮግራሞች ላይ ከኖቤል ኢንስቲትዩት ጋር በመነጋገር ይካፈላሉ" ብለዋል።
ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት ባሰራጨው መረጃ የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዝደንት ባራክ ኦባማ በ2009 የኖቤል የሰላም ሽልማት በተቀበሉበት ወቅት የሚድያ ፕሮግራሙ ላይ ሳይሳተፉ ቀርተው እንደነበር አስውሷል።
(ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት)
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
"ጠ/ሚር አብይ የኖርዌይ እና የአለም አቀፍ ሚድያ ጋዜጠኞችን ቢያገኙ ምኞቴ ነበር"--- የኖቤል ኢንስቲትዩት ዳይሬክተር
"የኖቤል ሽልማት ፕሮግራም ረዥም/ሰፋ ያለ ነው። ለአንድ የሀገር መሪ ሁሉም ፕሮግራሞች ላይ መካፈል አስቸጋሪ ነው፣ በተለይ ሀገር ውስጥ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች ባሉበት ወቅት"--- የጠ/ሚሩ ፕረስ ሰክረታሪ ቢለኔ ስዩም
የኖርዌይ የኖቤል ኢንስቲትዩት ዳይሬክተር ኦላቭ ጆልስታድ ጠ/ሚር አብይ ከአምስት ቀን በሁዋላ ሽልማታቸውን በሚቀበሉበት ወቅት ጥያቄዎች የሚጠየቁበት ፕሮግራም ላይ እንደማይገኙ ገልፀው "ይህ በጣም ችግር ነው። ጠ/ሚር አብይ የኖርዌይ እና የአለም አቀፍ ሚድያ ጋዜጠኞችን ቢያገኙ ምኞቴ ነበር" ብለው ለአሶሼትድ ፕረስ ተናግረዋል።
ዛሬ የጠ/ሚሩ ፕረስ ሰክረታሪ ቢለኔ ስዩም ለAssociated Press ጋዜጠኛው ኤልያስ መሰረት በሰጡት መረጃ - "የኖቤል ሽልማት ፕሮግራም ረዥም/ሰፋ ያለ ነው። ለአንድ የሀገር መሪ ሁሉም ፕሮግራሞች ላይ መካፈል አስቸጋሪ ነው፣ በተለይ ሀገር ውስጥ ትኩረት የሚሹ ጉዳዮች ባሉበት ወቅት። ስለዚህ ጠ/ሚሩ በተመረጡ እና ቅድሚያ በሚሰጣቸው ፕሮግራሞች ላይ ከኖቤል ኢንስቲትዩት ጋር በመነጋገር ይካፈላሉ" ብለዋል።
ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት ባሰራጨው መረጃ የቀድሞው የአሜሪካ ፕሬዝደንት ባራክ ኦባማ በ2009 የኖቤል የሰላም ሽልማት በተቀበሉበት ወቅት የሚድያ ፕሮግራሙ ላይ ሳይሳተፉ ቀርተው እንደነበር አስውሷል።
(ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት)
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
2 ተማሪዎች ወረቀት ሲለጥፉ በዩኒቨርሲቲው የጥበቃ ሥራተኞች እና በክልሉ ልዮ ኃይሎች እጅ ከፍንጅ ተያዙ!
በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ህዳር 24/2012ዓ.ም ምሽት 1:30 ላይ ጠዳ ግቢ አንድን ብሄር ከሌላ ብሄር የሚያጋጭ ጽሑፍ ተበትኖና ተለጥፎ ወዲያው በጸጥታ ኃይሎች እንደተያዘ ዩኒቨርሲቲው ገልጿል። በተመሳሳይ ቀን ከምሽቱ 4:05 አካባቢ ሁለት ተማሪዎች ወረቀቱን ሲለጥፉ በዩኒቨርሲቲው የጥበቃ ሥራተኞች እና በክልሉ ልዮ ኃይሎች እጅ ከፍንጅ መያዛቸውን ዩኒቨርሲቲው አስታውቋል።
ተማሪዎች በሁሉም ግቢዎች ያለውን ሰላማዊ መማር ማስተማር የሚያውኩ ማንኛውም እንቅስቃሴ ከጸጥታና ደህንነት እይታ ውጭ አለመሆኑ እንዲያውቁት ያለው ተቋሙ እየተለየ ተልዕኮ ያላቸውን አካላት ከጥፋት ድርጊታቸው እንድትቆጠቡ አሳስቧል።
በቁጥጥር ሥር የዋሉ ተጠርጣሪ ተማሪዎች ጉዳያቸው ተጣርቶ ሲጠናቀቅ። ውጤቱን ለሚመለከተው ሁሉ እደሚያሳውቅ ዩኒቨርሲቲው ገልጿል። ሰላማዊ መማር ማስተማር ሂደቱ እንደተለመደው ይቀጥላልም ብሏል።
(ጎንደር ዩኒቨርሲቲ)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ህዳር 24/2012ዓ.ም ምሽት 1:30 ላይ ጠዳ ግቢ አንድን ብሄር ከሌላ ብሄር የሚያጋጭ ጽሑፍ ተበትኖና ተለጥፎ ወዲያው በጸጥታ ኃይሎች እንደተያዘ ዩኒቨርሲቲው ገልጿል። በተመሳሳይ ቀን ከምሽቱ 4:05 አካባቢ ሁለት ተማሪዎች ወረቀቱን ሲለጥፉ በዩኒቨርሲቲው የጥበቃ ሥራተኞች እና በክልሉ ልዮ ኃይሎች እጅ ከፍንጅ መያዛቸውን ዩኒቨርሲቲው አስታውቋል።
ተማሪዎች በሁሉም ግቢዎች ያለውን ሰላማዊ መማር ማስተማር የሚያውኩ ማንኛውም እንቅስቃሴ ከጸጥታና ደህንነት እይታ ውጭ አለመሆኑ እንዲያውቁት ያለው ተቋሙ እየተለየ ተልዕኮ ያላቸውን አካላት ከጥፋት ድርጊታቸው እንድትቆጠቡ አሳስቧል።
በቁጥጥር ሥር የዋሉ ተጠርጣሪ ተማሪዎች ጉዳያቸው ተጣርቶ ሲጠናቀቅ። ውጤቱን ለሚመለከተው ሁሉ እደሚያሳውቅ ዩኒቨርሲቲው ገልጿል። ሰላማዊ መማር ማስተማር ሂደቱ እንደተለመደው ይቀጥላልም ብሏል።
(ጎንደር ዩኒቨርሲቲ)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ለዩኒቨርሲቲ መምህራንና ተማሪዎች የሰላም ጥሪ ቀረበ!
የአማራና የኦሮሞ የሃይማኖት አባቶች፣የአገር ሽማግሌዎችና ታዋቂ ሰዎች ለዩኒቨርሲቲ መምህራንና ተማሪዎች የሰላም ጥሪ አቀረቡ። የሃይማኖት አባቶች ፣የአገር ሽማግሌዎችና ታዋቂ ሰዎች ዛሬ በአዲስ አበባ ባደረጉት የሰላም ጥሪ አሁንም በከፍተኛ የትምህረት ተቋማት ትምህርታቸውን ያልጀመሩ ተማሪዎች እንዳሉ ገልጸዋል።
እነዚህ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታቸው ገብተው ሰላማዊ የመማር ማስተማሩን ሂደት እንዲቀጥሉ የሃይማኖት አባቶች፣ የአገር ሽማግሌዎችና ታዋቂ ሰዎቹ ጥሪ አስተላልፈዋል። በተለይ በአሁኑ ወቅት አብዛኛው ዩኒቨርስቲዎች ወደትምህርት ገበታቸው የተመለሱ መሆኑን የጠቀሱት የሃገር ሽማግሌዎቹ ሌሎቹም ይህንን ጥሪ ተከትለው ወደሰላማዊ የመማር ማስተማሩ ሂደት እንዲገቡ ጥሪ አቅርበዋል።
አንዳንድ ግለሰቦችም ተማሪዎችን ለፖለቲካ መጠቀሚያ እያደረጓቸው እንደሆነም ታውቋል፤እነዚህም ግለሰቦች ከዚህ ድርጊታቸው እንዲቆጠቡ የሃይማኖት አባቶች አሳስበዋል። በትምህርት ገበታቸው ያልተገኙ ተማሪዎች ጊዜያቸውን በአግባቡ እንዲጠቀሙና ወደትክክለኛ የመማር ማስተማር ሂደት እንዲገቡ ጥሪ አስተላልፈዋል።
መምህራንም የነገ የታሪክ ተወቃሽ እንዳይሆኑ ተማሪዎችን በአግባቡ በማረቅ ኃላፊነታቸውን ይወጡ ዘንድም አሳስበዋል። የሃይማኖት አባቶች፣ የአገር ሽማግሌዎች፣ ታዋቂ ሰዎች የተውጣው አብይ ኮሚቴዎች ወደ መማር ማስተማሩ ያልገቡ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት መምህራን፣ ተማሪ እና የአካባቢ ነዋሪዎችን ያወያያሉ።
(ENA)
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
የአማራና የኦሮሞ የሃይማኖት አባቶች፣የአገር ሽማግሌዎችና ታዋቂ ሰዎች ለዩኒቨርሲቲ መምህራንና ተማሪዎች የሰላም ጥሪ አቀረቡ። የሃይማኖት አባቶች ፣የአገር ሽማግሌዎችና ታዋቂ ሰዎች ዛሬ በአዲስ አበባ ባደረጉት የሰላም ጥሪ አሁንም በከፍተኛ የትምህረት ተቋማት ትምህርታቸውን ያልጀመሩ ተማሪዎች እንዳሉ ገልጸዋል።
እነዚህ ተማሪዎች ወደ ትምህርት ገበታቸው ገብተው ሰላማዊ የመማር ማስተማሩን ሂደት እንዲቀጥሉ የሃይማኖት አባቶች፣ የአገር ሽማግሌዎችና ታዋቂ ሰዎቹ ጥሪ አስተላልፈዋል። በተለይ በአሁኑ ወቅት አብዛኛው ዩኒቨርስቲዎች ወደትምህርት ገበታቸው የተመለሱ መሆኑን የጠቀሱት የሃገር ሽማግሌዎቹ ሌሎቹም ይህንን ጥሪ ተከትለው ወደሰላማዊ የመማር ማስተማሩ ሂደት እንዲገቡ ጥሪ አቅርበዋል።
አንዳንድ ግለሰቦችም ተማሪዎችን ለፖለቲካ መጠቀሚያ እያደረጓቸው እንደሆነም ታውቋል፤እነዚህም ግለሰቦች ከዚህ ድርጊታቸው እንዲቆጠቡ የሃይማኖት አባቶች አሳስበዋል። በትምህርት ገበታቸው ያልተገኙ ተማሪዎች ጊዜያቸውን በአግባቡ እንዲጠቀሙና ወደትክክለኛ የመማር ማስተማር ሂደት እንዲገቡ ጥሪ አስተላልፈዋል።
መምህራንም የነገ የታሪክ ተወቃሽ እንዳይሆኑ ተማሪዎችን በአግባቡ በማረቅ ኃላፊነታቸውን ይወጡ ዘንድም አሳስበዋል። የሃይማኖት አባቶች፣ የአገር ሽማግሌዎች፣ ታዋቂ ሰዎች የተውጣው አብይ ኮሚቴዎች ወደ መማር ማስተማሩ ያልገቡ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት መምህራን፣ ተማሪ እና የአካባቢ ነዋሪዎችን ያወያያሉ።
(ENA)
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
'THE GUARDIAN' ኢትዮጵያዊውን ጋዜጠኛ መርጧል!
የ እንግሊዙ ተነባቢው ድህረ-ገፅ THE GUARDIAN የአመቱ መቶ ምርጥ ሴት ተጫዋቾች ይፋ ሲያደርግ በዳኝነት 93 የቀድሞ ተጫዋቾች፣ አሰልጣኞች እና ጋዜጠኞችን ከተለያዩ የአለም ሃገራት አካቷል ::
ስምንት አፍራካዊያንን THE GUARDIAN ለዳኝነት ሲመርጥ ኢትዮጵያዊው የስፖርት ፀሃፊ እና የቲኪቫህ ስፖርት ቤተሰብ እንዲሁም የተለያዩ ጠቃሚ ትንታኔዎችን ወደ እናንተ የሚያደርሰው ፍሬው አስራት ከሌሎች ሰባት አፍራካዊያን ጋር በመሆን የድምፅ ሰጪው ፓናል አባል ነበረ።
Join👇
@tikvahethsport
https://t.iss.one/joinchat/AAAAAFb8M0pNEZTiGM68rg
የ እንግሊዙ ተነባቢው ድህረ-ገፅ THE GUARDIAN የአመቱ መቶ ምርጥ ሴት ተጫዋቾች ይፋ ሲያደርግ በዳኝነት 93 የቀድሞ ተጫዋቾች፣ አሰልጣኞች እና ጋዜጠኞችን ከተለያዩ የአለም ሃገራት አካቷል ::
ስምንት አፍራካዊያንን THE GUARDIAN ለዳኝነት ሲመርጥ ኢትዮጵያዊው የስፖርት ፀሃፊ እና የቲኪቫህ ስፖርት ቤተሰብ እንዲሁም የተለያዩ ጠቃሚ ትንታኔዎችን ወደ እናንተ የሚያደርሰው ፍሬው አስራት ከሌሎች ሰባት አፍራካዊያን ጋር በመሆን የድምፅ ሰጪው ፓናል አባል ነበረ።
Join👇
@tikvahethsport
https://t.iss.one/joinchat/AAAAAFb8M0pNEZTiGM68rg
ዮዌሪ ሙሴቬኒ የመሩት የጸረ ሙስና ሰልፍ!
የዩጋንዳ ፕሬዚዳንት ዮዌሪ ሙሴቬኒ በትናንትናው ዕለት በመሩት ጸረ ሙስና ሰልፍ ላይ ሙሰኞች የህዝብን ሃብት የሚመጠምጡቱ ተውሳኮች ናቸው ሲሉ ተናገሩ።
የዩጋንዳ ፕሬዚዳንት ዮዌሪ ሙሴቬኒ ነቃፊዎች ግን ፈጥነው ይሄ ለታይታ እንጂ ሌላ ትርጉም የለውም ብለዋል፡፡ ዩጋንዳ በዓለም ላይ በከፋ ደረጃ በሙስኛ ከዘቀጡ ሃገሮች መካከል የምትጠራ ስትሆን ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናት ላይ ጣታቸውን ይቀስራሉ፡፡
ትራንስፓረንሲ ኢንተርናሺናል በአምና ሪፖርቱ ዩጋንዳን ሙስና በከፋ ሁኔታ ከተንሰራፋባቸው የአፍሪካ ሃገሮች አንዱዋ አድርጎ አስቀምጧታል።
አክሺን ኤይድ የተባለው ግብረ ሰናይ ድርጅትም በአብዛኛው ተጠያቂው መንግሥታቸው ሆኖ ሳለ የእርሳቸው ጸረ ሙስና ሰልፍ መምራት የሚገርም ነው ብሎታል፡፡
(VOA)
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
የዩጋንዳ ፕሬዚዳንት ዮዌሪ ሙሴቬኒ በትናንትናው ዕለት በመሩት ጸረ ሙስና ሰልፍ ላይ ሙሰኞች የህዝብን ሃብት የሚመጠምጡቱ ተውሳኮች ናቸው ሲሉ ተናገሩ።
የዩጋንዳ ፕሬዚዳንት ዮዌሪ ሙሴቬኒ ነቃፊዎች ግን ፈጥነው ይሄ ለታይታ እንጂ ሌላ ትርጉም የለውም ብለዋል፡፡ ዩጋንዳ በዓለም ላይ በከፋ ደረጃ በሙስኛ ከዘቀጡ ሃገሮች መካከል የምትጠራ ስትሆን ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናት ላይ ጣታቸውን ይቀስራሉ፡፡
ትራንስፓረንሲ ኢንተርናሺናል በአምና ሪፖርቱ ዩጋንዳን ሙስና በከፋ ሁኔታ ከተንሰራፋባቸው የአፍሪካ ሃገሮች አንዱዋ አድርጎ አስቀምጧታል።
አክሺን ኤይድ የተባለው ግብረ ሰናይ ድርጅትም በአብዛኛው ተጠያቂው መንግሥታቸው ሆኖ ሳለ የእርሳቸው ጸረ ሙስና ሰልፍ መምራት የሚገርም ነው ብሎታል፡፡
(VOA)
@tikvahethiopia @tikvahethiopiaBot
መንግስት ሳያውቅ ቀርቶ ነው?
(ቲክቫህ ኢትዮጵያ)
ለመሆኑ የት የት ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ትምህርት እንዳልተጀመረ፣ የተወሰኑ ተማሪዎች እየተለዩ እንዳይማሩ ማስፈራሪያና መስጠንቀቂያ እንደሚደርሳቸው፣ የትኞቹ ግቢዎች ውስጥ የማስፈራሪያ ወረቀቶች እንደሚለጠፉ፤ እንደሚበተኑ፣ የት የት ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ተማሪዎች በከፍተኛ ስጋት ውስጥ እንዳሉ፣ ከየት የት ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎች ግቢያቸውን ለቀው ወጥተው ወደ ቤተሰቦቻቸው የሄዱ፣ያልቻሉ ደግሞ በየሰው ቤት እና በየእምነት ተቋማት እንዳሉ፣ በየትኛው ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ዛሬም በሚሰራጩ የማስፈራሪያ ፅሁፎች ተማሪዎች ሰግተው ከማደሪያቸው ወጥተው ውጭ እንዳሉ...የዩኒቨርሲቲ አስተዳደሮች፣ ከፍተኛ አመራሮች አያውቁም? ሀገሪቷን እያስተዳደረው የሚገኘው መንግስት አያውቅም?
ዩኒቨርሲቲዎችን የሚያሰተዳድረው አካል አያውቅም? መንግስት ይህ ሁሉ ሲደረግ፣ የማስፈራሪያ ፅሁፍ እንደልብ ሲሰራጭ፣ እከሌ ተማር እከሌ ውጣ ሲባል ቁጭ ብሎ ነው የሚመለከተው? የክልል መንግስታት የተማሪዎችን ሁኔታ ሳያውቁ ቀርተው ነው? ተማሪዎችን የሚያስፈራሩ ከህግ በላይ የሆኑ ሰዎች እንዲህ ሲፈነጩ ምን እስኪሆን እየጠበቀ ነው? መፍትሄ መስጠት ስለማይቻል ነው? ካልተቻለ ተማሪ በዚህ ሁኔታ እንዲማር ማስገደድ ምን የሚሉት አሰራር ነው? ተማሪው እና ወላጆች የዚህ አይነት ሁኔታ ሲገጥማቸው፣ችግሮች ቶሎ ካልተፈቱላቸው በሀገራቸው ተስፋ እንዲቆርጡ እንደሚያደርግ፤በመንግስት ላይም እምነት እንዲያጡ እንደሚያደርግ ሳይታወቅ ቀርቶ ነው?
ባለፉትን ሳምንታት የት የት ችግር እንደነበረ በየዕለቱ እየገለፅን ስንጮህ ነበር። ከቀን ወደ ቀን ሁሉም ነገር ወደ መደበኛ ሁኔታ ይመለሳል ብለን ስንከታተል ችግሩ በዘላቂነት ሳይፈታ ዛሬ ላይም የስጋት መልዕክቶች መቀበላችን ቀጥለናል!
@tikvahethiopiaBot
(ቲክቫህ ኢትዮጵያ)
ለመሆኑ የት የት ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ትምህርት እንዳልተጀመረ፣ የተወሰኑ ተማሪዎች እየተለዩ እንዳይማሩ ማስፈራሪያና መስጠንቀቂያ እንደሚደርሳቸው፣ የትኞቹ ግቢዎች ውስጥ የማስፈራሪያ ወረቀቶች እንደሚለጠፉ፤ እንደሚበተኑ፣ የት የት ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ተማሪዎች በከፍተኛ ስጋት ውስጥ እንዳሉ፣ ከየት የት ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎች ግቢያቸውን ለቀው ወጥተው ወደ ቤተሰቦቻቸው የሄዱ፣ያልቻሉ ደግሞ በየሰው ቤት እና በየእምነት ተቋማት እንዳሉ፣ በየትኛው ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ ዛሬም በሚሰራጩ የማስፈራሪያ ፅሁፎች ተማሪዎች ሰግተው ከማደሪያቸው ወጥተው ውጭ እንዳሉ...የዩኒቨርሲቲ አስተዳደሮች፣ ከፍተኛ አመራሮች አያውቁም? ሀገሪቷን እያስተዳደረው የሚገኘው መንግስት አያውቅም?
ዩኒቨርሲቲዎችን የሚያሰተዳድረው አካል አያውቅም? መንግስት ይህ ሁሉ ሲደረግ፣ የማስፈራሪያ ፅሁፍ እንደልብ ሲሰራጭ፣ እከሌ ተማር እከሌ ውጣ ሲባል ቁጭ ብሎ ነው የሚመለከተው? የክልል መንግስታት የተማሪዎችን ሁኔታ ሳያውቁ ቀርተው ነው? ተማሪዎችን የሚያስፈራሩ ከህግ በላይ የሆኑ ሰዎች እንዲህ ሲፈነጩ ምን እስኪሆን እየጠበቀ ነው? መፍትሄ መስጠት ስለማይቻል ነው? ካልተቻለ ተማሪ በዚህ ሁኔታ እንዲማር ማስገደድ ምን የሚሉት አሰራር ነው? ተማሪው እና ወላጆች የዚህ አይነት ሁኔታ ሲገጥማቸው፣ችግሮች ቶሎ ካልተፈቱላቸው በሀገራቸው ተስፋ እንዲቆርጡ እንደሚያደርግ፤በመንግስት ላይም እምነት እንዲያጡ እንደሚያደርግ ሳይታወቅ ቀርቶ ነው?
ባለፉትን ሳምንታት የት የት ችግር እንደነበረ በየዕለቱ እየገለፅን ስንጮህ ነበር። ከቀን ወደ ቀን ሁሉም ነገር ወደ መደበኛ ሁኔታ ይመለሳል ብለን ስንከታተል ችግሩ በዘላቂነት ሳይፈታ ዛሬ ላይም የስጋት መልዕክቶች መቀበላችን ቀጥለናል!
@tikvahethiopiaBot
ከ6 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የአራት መንገድ ፕሮጀክት ግንባታ ሥራ የውል ስምምነት ተፈረመ!
ከ6 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ 299 ኪሎ ሜትር ርዝመት የሚሸፍኑ የአራት መንገድ ፕሮጀክት ግንባታ ሥራ የውል ስምምነት ተፈረመ፡፡ በዛሬው ዕለት የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሀብታሙ ተገኝ እና ሌሎች የስራ ኃላፊዎች፣ የፓርላማ አባላት፣ ከአራቱም የመንገድ የፕሮጀክት የመጡ የህዝብ ተወካዮች በተገኙበት 299 ኪሎ ሜትር ርዝመት የሚሸፍኑ የአራት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶች ከ6 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ከአሽናፊ የስራ ተቋራጮች ጋር በኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን የመሰብሰቢያ አዳራሽ ተፈርሟል። የተፈረሙት አራት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶች የሃሙሲት - እስቴ፣ ጩለሴ - ሶያማ፣ የአደሌ - ግራዋ እና የጎዴ - ቀላፎ መሆናቸውን ከኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን የተገኘው መረጃ ይጠቁማል።
(ERA)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ከ6 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ 299 ኪሎ ሜትር ርዝመት የሚሸፍኑ የአራት መንገድ ፕሮጀክት ግንባታ ሥራ የውል ስምምነት ተፈረመ፡፡ በዛሬው ዕለት የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሀብታሙ ተገኝ እና ሌሎች የስራ ኃላፊዎች፣ የፓርላማ አባላት፣ ከአራቱም የመንገድ የፕሮጀክት የመጡ የህዝብ ተወካዮች በተገኙበት 299 ኪሎ ሜትር ርዝመት የሚሸፍኑ የአራት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶች ከ6 ነጥብ 1 ቢሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ከአሽናፊ የስራ ተቋራጮች ጋር በኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን የመሰብሰቢያ አዳራሽ ተፈርሟል። የተፈረሙት አራት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቶች የሃሙሲት - እስቴ፣ ጩለሴ - ሶያማ፣ የአደሌ - ግራዋ እና የጎዴ - ቀላፎ መሆናቸውን ከኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን የተገኘው መረጃ ይጠቁማል።
(ERA)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#LemmaMegersa
አሜሪካ - ኢትዮጵያ ለቀጠናው ሰላም እያበረከተች ያለውን በጎ ሚና አደነቀች!
የኢፌዴሪ መከላከያ ሚኒስትር አቶ ለማ መገርሳ ከአሜሪካ የመከላከያ ሚኒስቴር ከፍተኛ ኃላፊዎች ጋር በዋሽንግተን ዲሲ የተወያዩ ሲሆን፣ በውይይቱ ላይ የአሜሪካ የመከላከያ ሚኒስቴር ኃላፊዎች ኢትዮጵያ በቀጣናው ሰላም የሚታበረክተው በጎ ሚና እና በመከላከያ ዘርፍ የምታካሄደውን ማሻሻያ አድንቀዋል፡፡ የሁለቱ አገራት 9ኛው የሁለትዮሽ የመከላከያ ኮሚቴ ዓመታዊ ስብሰባ በዋሽንግተን ከተማ ተካሂዷል።
በስብሰባው ሁለቱ አገራት በቀጣናው የጸጥታና ደህንነት፣ የመረጃ፣ ሰላም ማስከበር እና መከላከያ ጉዳዮች ዙሪያ ገምቢ ምክክር ያደረጉ ሲሆን፣ ይህም የአገራቱን በጸጥታና ደህንነት ዙሪያ ያላቸውን ትብብር የበለጠ እንደሚያጎለብት ተገልጿል፡፡
አገራቱ የሁለትዮሽ ግንኙነቱ የበለጠ እንዲጠናከር ያላቸውን ቁርጠኝነት የገለጹ ሲሆን፣ ባለፉት 18 ወራት በጸጥታው ዘርፍ እያደገ የመጣው ትብብርም ለዚህ ማሳያ እንደሆነ ነው የተገለጸው። የሁለትዮሽ የመከላከያ ኮሚቴ ስብሰባው ኢትዮጵያና አሜሪካ ያላቸውን ጠንካራ ግንኙነት በማበልጸግ በጸረ ሽብር፣ በደህንነት መረጃ እና ሌሎች የትብብር ዘርፎችን በመለየት በምስራቅ አፍሪካ ቀጣና ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን ለማድረግ እንደሚያስችላቸው ከአሜሪካ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡
(ኢቢሲ)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
አሜሪካ - ኢትዮጵያ ለቀጠናው ሰላም እያበረከተች ያለውን በጎ ሚና አደነቀች!
የኢፌዴሪ መከላከያ ሚኒስትር አቶ ለማ መገርሳ ከአሜሪካ የመከላከያ ሚኒስቴር ከፍተኛ ኃላፊዎች ጋር በዋሽንግተን ዲሲ የተወያዩ ሲሆን፣ በውይይቱ ላይ የአሜሪካ የመከላከያ ሚኒስቴር ኃላፊዎች ኢትዮጵያ በቀጣናው ሰላም የሚታበረክተው በጎ ሚና እና በመከላከያ ዘርፍ የምታካሄደውን ማሻሻያ አድንቀዋል፡፡ የሁለቱ አገራት 9ኛው የሁለትዮሽ የመከላከያ ኮሚቴ ዓመታዊ ስብሰባ በዋሽንግተን ከተማ ተካሂዷል።
በስብሰባው ሁለቱ አገራት በቀጣናው የጸጥታና ደህንነት፣ የመረጃ፣ ሰላም ማስከበር እና መከላከያ ጉዳዮች ዙሪያ ገምቢ ምክክር ያደረጉ ሲሆን፣ ይህም የአገራቱን በጸጥታና ደህንነት ዙሪያ ያላቸውን ትብብር የበለጠ እንደሚያጎለብት ተገልጿል፡፡
አገራቱ የሁለትዮሽ ግንኙነቱ የበለጠ እንዲጠናከር ያላቸውን ቁርጠኝነት የገለጹ ሲሆን፣ ባለፉት 18 ወራት በጸጥታው ዘርፍ እያደገ የመጣው ትብብርም ለዚህ ማሳያ እንደሆነ ነው የተገለጸው። የሁለትዮሽ የመከላከያ ኮሚቴ ስብሰባው ኢትዮጵያና አሜሪካ ያላቸውን ጠንካራ ግንኙነት በማበልጸግ በጸረ ሽብር፣ በደህንነት መረጃ እና ሌሎች የትብብር ዘርፎችን በመለየት በምስራቅ አፍሪካ ቀጣና ዘላቂ ሰላም እንዲሰፍን ለማድረግ እንደሚያስችላቸው ከአሜሪካ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡
(ኢቢሲ)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#INSA
የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ ለቀይ መስቀል የቢሮ መገልገያዎችን ድጋፍ አደረገ። ዛሬ ህዳር 25 ቀን 2012 ዓ.ም የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ ለቀይ መስቀል ለቢሮ አገልግሎት የሚውሉ 50 ኮምፒውተሮች፣ 28 የሀላፊ ወንብሮች ፣ ጠረጴዛ እና ሌሎች ቁሳቁሶችን ድጋፍ አድርጋል። ድጋፉ በገንዘብ ሲተመን ወደ 400,000 /አራት መቶ ሺህ ብር/ የሚገመት ነው። ይህ ድጋፍ ቀይ መስቀል ለሚሰጠው አገልግሎት መጠናከር አይነተኛ አስተዋፅዖ ያለው በመሆኑ ለተቋሙ በአገልግሎታችን ተጠቃሚዎች ስም ከፍ ያለ ምስጋናችንን እናቀርባለን የሚል መልዕክት በቲክቫ ኢትዮጵያ በኩል እንዲደርሳቸው መልእክቱን ያስተላልፈዋል።
ህዝብ የቀይ መስቀል መስረት ነው!
የቀይ መስቀል አባል በመሆን ይመዝገቡ!
ለሰብአዊነት እንኖራለን!
(ማንደፍሮ ነጋሽ)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ ለቀይ መስቀል የቢሮ መገልገያዎችን ድጋፍ አደረገ። ዛሬ ህዳር 25 ቀን 2012 ዓ.ም የኢንፎርሜሽን መረብ ደህንነት ኤጀንሲ ለቀይ መስቀል ለቢሮ አገልግሎት የሚውሉ 50 ኮምፒውተሮች፣ 28 የሀላፊ ወንብሮች ፣ ጠረጴዛ እና ሌሎች ቁሳቁሶችን ድጋፍ አድርጋል። ድጋፉ በገንዘብ ሲተመን ወደ 400,000 /አራት መቶ ሺህ ብር/ የሚገመት ነው። ይህ ድጋፍ ቀይ መስቀል ለሚሰጠው አገልግሎት መጠናከር አይነተኛ አስተዋፅዖ ያለው በመሆኑ ለተቋሙ በአገልግሎታችን ተጠቃሚዎች ስም ከፍ ያለ ምስጋናችንን እናቀርባለን የሚል መልዕክት በቲክቫ ኢትዮጵያ በኩል እንዲደርሳቸው መልእክቱን ያስተላልፈዋል።
ህዝብ የቀይ መስቀል መስረት ነው!
የቀይ መስቀል አባል በመሆን ይመዝገቡ!
ለሰብአዊነት እንኖራለን!
(ማንደፍሮ ነጋሽ)
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
#Day3 #አርባምንጭ #ዊዝደምአካዳሚ
"የነገ ተስፋችሁ እኛነንና ፍቅርን አስተምሩን"
ዛሬ ከሰዓት በኃላ በነበረን መርኃግብር "በዊዝደም አካዳሚ ከአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት" ተማሪዎች ጋር ጥሩ ጊዜ አሳልፈናል። ተማሪዎቹ ልዩ ልዩ የባህል ፕሮግራሞችን አዘጋጅተው የጠበቁን ሲሆን በህጻናት ግጥሞች ቀርበዋል፡፡ በዝግጅቱ ላይ አባቶች ተገኝተው ልጆቹን የመረቁ ሲሆን የአርባ ምንጭ የህክምና ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተመራቂ ተማሪዎች ለተማሪዎቹ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
#ቲክቫህኢትዮጵያ #ፒስሞዴል #ጋሞዞን
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
"የነገ ተስፋችሁ እኛነንና ፍቅርን አስተምሩን"
ዛሬ ከሰዓት በኃላ በነበረን መርኃግብር "በዊዝደም አካዳሚ ከአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት" ተማሪዎች ጋር ጥሩ ጊዜ አሳልፈናል። ተማሪዎቹ ልዩ ልዩ የባህል ፕሮግራሞችን አዘጋጅተው የጠበቁን ሲሆን በህጻናት ግጥሞች ቀርበዋል፡፡ በዝግጅቱ ላይ አባቶች ተገኝተው ልጆቹን የመረቁ ሲሆን የአርባ ምንጭ የህክምና ትምህርት ቤት የዘንድሮ ተመራቂ ተማሪዎች ለተማሪዎቹ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
#ቲክቫህኢትዮጵያ #ፒስሞዴል #ጋሞዞን
@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ተስፋችሁ እኛ ነን፤ ፍቅር አስተምሩን!
አርባ ምንጭ❤️ዊዝደም አካዳሚ❤️
እነዚህ ትንንሽ የነገ ሀገር ተረካቢዎች ስናይ ተስፋችን ተሟጦ እንዳላለቀ በደንብ እንገነዘባለን። ለተተኪው ትውልዱ ከቂም፣ ከክፋት፣ ከተንኮል፣ከመገፋፋት፣ ከጥላቻነፃ የሆነች ሀገር የማስረከብ ግዴታ አለብን። ለነዚህ ሀገር ተረካቢ ልጆች ፍቅር፣ መዋደድን፣ መተባበርን፣ መደጋገፍን የማስተማር ግዴታ አለበን።
#ቲክቫህኢትዮጵያ #ፒስሞዴል #ኡቡንቱ #Day3
ውድ ቤተሰቦቻችን ማንኛው አይነት ሃሳብ፣ አስተያየት እና መልዕክት ካላችሁ በ @tsegabwolde ወይም በ @tikvahethiopiaBot ላይ ማድረስ ትችላላችሁ!
@tikvahethiopia
አርባ ምንጭ❤️ዊዝደም አካዳሚ❤️
እነዚህ ትንንሽ የነገ ሀገር ተረካቢዎች ስናይ ተስፋችን ተሟጦ እንዳላለቀ በደንብ እንገነዘባለን። ለተተኪው ትውልዱ ከቂም፣ ከክፋት፣ ከተንኮል፣ከመገፋፋት፣ ከጥላቻነፃ የሆነች ሀገር የማስረከብ ግዴታ አለብን። ለነዚህ ሀገር ተረካቢ ልጆች ፍቅር፣ መዋደድን፣ መተባበርን፣ መደጋገፍን የማስተማር ግዴታ አለበን።
#ቲክቫህኢትዮጵያ #ፒስሞዴል #ኡቡንቱ #Day3
ውድ ቤተሰቦቻችን ማንኛው አይነት ሃሳብ፣ አስተያየት እና መልዕክት ካላችሁ በ @tsegabwolde ወይም በ @tikvahethiopiaBot ላይ ማድረስ ትችላላችሁ!
@tikvahethiopia