TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.4K photos
1.51K videos
215 files
4.12K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#UPDATE

ከባሕር ዳር ወደ አዲስ አበባ የሚጓዙ ተሽከርካሪዎች ጎሃፅዮን ላይ መንገድ በመዘጋቱ እንዳናልፍ ተደርገናል ሲሉ ለአሐዱ ተናገሩ፡፡ የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን በበኩሉ እሁድ በአዲስ አበባ ይደረጋል በተባለው ሰልፍ ስጋት መንገዱ መዘጋቱን ገልጿል፡፡

አርብ ከማለዳ 3 ሰዓት ጀምሮ በኦሮሚያ ፀጥታ አካላት ከባሕር ዳር መስመር የሚመጡ ተሽከርካሪዎች ወደ አዲስ አበባ እንዳይገቡ ጎሃፅዮን ላይ መታገዳቸውን አሽከርካሪዎች ለአሐዱ ቴሌቪዥን ተናግረዋል፡፡ በተከለከሉት ተሽከርካሪዎቹ ውስጥ ወደ ተለያዩ ዩኒቨርስቲዎች የሚሄዱ በርካታ ተማሪዎች መኖራቸውን የገለፁት አሽከርካሪዎቹ፤ መንገድ በመዘጋቱ ምክንያት ወደ መጡበት ለመመለስ መገደዳቸውን ገልጸዋል፡፡

አሐዱ ቴሌቪዥን መረጃ የጠየቃቸው የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ኮማንደር ደረጀ ፈጠነ መንገዱ እሁድ በአዲስ አበባ ከተማ የተጠራ ሰላማዊ ሰልፍ ምክንያት ስጋቶች በመኖራቸው መዘጋቱን ገልፀዋል፡፡ መንገዱን ዘግቷል የተባለው የወረጃርሶ ፖሊስ በኬላው ላይ በሚደረግ ፍተሻ በተፈጠረ መጨናነቅ እንጂ የተዘጋ መንገድ የለም ሲል አስተባብሏል፡፡

ፖሊስ የፀጥታ ስጋት በአካባቢው አለ መባሉን ተከትሎ ፍተሻ እያደረገ መሆኑን የወረጃርሶ ፖሊስ ኃላፊ ኢንስፔክተር መንግሥት ከተማ ገልፀዋል፡፡ ይሁንና ተጓዦች ለተለያዩ እንግልቶች መዳረጋቸውን በመግለጽ ፌደራሉ መንግሥት ጣልቃ እንዲገባ ጠይቀዋል፡፡

ምንጭ፦ አሃዱ ቴሌቪዥን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#AddisAbeba

የቤቶች ልማት እና አስተዳደር ቢሮ በከተማዋ አዲስ በሚጀመሩ ቤቶች ግንባታ ዙሪያ ለጋዜጠኞች መግለጫ ሰቷዋል፡፡ የቢሮው ኃላፊ ኢ/ር ሰናይት ዳምጠው የከተማ አስተዳደሩ በ2012 ቀደም ሲል ከነበሩ ዲዛይኖች ላይ መጠነኛ ማሻሻያ በማድረግ 500ሺ መኖሪያ ቤቶችን በከተማው ለማስገንባት በተለያዩ የግንባታ አማራጮችን ይዞ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን ገልፀዋል፡፡

በዚህም ፦

1. በመንግስት የሚገነቡ 150 ሺ ቤቶችን በ20/80 እና 40/60 ፕሮግራም ተመዝግበው ለሚገኙ የሚነገቡ ይሆናል፡፡

2. በ75 ሄክታር መሬት ላይ 25 ሺ ኪራይ ቤቶች ግንባታ፡፡ ለዚህኛው በተለየ መልኩ በ10ሩም ክፍለ ከተሞች መታደስ እና መቀየር የሚገባቸውን የቀበሌ ቤቶች የሚገኙበትን ይዞታ በመጠቀም የሚገነባ ይሆናል፡፡ በዚህም መሠረት የፓይለት ስራው በሁለት ክፍለ ከተሞች ተጀምሯል፡፡

3. የከተማዋ ኪስ ቦታዎች በመጠቀም የ175 ሺ የማህበር ቤቶች ግንባታ በማካሄድ ነዋሪዎችን ተጠቃሚ ማድረግ

4. ባለሃብቶችን በማሳተፍ አቅም ላላቸው ነዋሪዎች የአፓርታማዎችን ግንባታ ማከናወን፡፡ ከተለያዩ የሃገር ውስጥ እና የውጪ ሃገር ባለሃብቶች ጋር በመሆን በተያዘው ዓመት 25 ሺ ቤቶችን ለመገንባት ዕቅድ ተይዟል፡፡

5. ከሪል ስቴት አልሚዎች ጋር በመሆን 75 ሺ ቤቶች ግንባታ ይጀመራል፡፡

ከላይ የተጠቀሱት የግንባታ አማራጮችን በ2012 ዓ.ም በመጀመር በዓመቱ መጨረሻ የግንባታዎቹን 30% ለማጠናቀቅ ይሰራል፡፡ በተጨማሪም በግንባታ ላይ የሚገኙ 139 ሺ በላይ ቤቶች ግንባታቸውን በማጠናቀቅ ለነዋሪዎች የሚተላለፉ ይሆናል፡፡ ከ90 ሺ በላይ የሚሆኑ የከተማዋ ወጣቶች በግንባታው የስራ ዕድል ያገኛሉ፡፡

Via Mayor Office AA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#NobelPeacePrize

የኢ.ፌ.ዴ.ሪ ትምህርት ሚኒስቴር ሚንስትር ዴኤታ ክብርት ወይዘሮ ፅዮን ተክሉ ለTIKVAH-ETH በላኩት መልዕክት ክቡር ጠቅላይ ሚንስትር ዶ/ር አብይ አህመድ የ2019 የኖቤል የሰላም ሽልማት አሸናፊ መሆናቸውን በማስመልከት በኢ.ፌ.ዴ.ሪ ትምህርት ሚኒስቴር እና በ "እኛ ለእኛ" የኢትዮጵያውያን በጎ ፍቃደኞች መርሃ ግብር ስም የእንኳን ደስ ያልዎት መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
Audio
ወ/ሮ ፅዮን ተክሉ - የትምህርት ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ! #NobelPeacePrize

#TikvahEthiopia
#NobelPeacePrize

የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዝደንት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሀጅ ኡመር ኢድርስ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ የኖቤል የሰላም ሽልማት በማግኘታቸው የእንኳን ደስ አልዎት መልዕክት አስተላፉ፡፡

ተቀዳሚ ሙፍቲ ሀጅ ኡመር ኢድሪስ ለFBC እንደተናገሩት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወደ ስልጣን ከመጡ ወዲህ የሰሯቸዉ ስራዎች ከዚህም በላይ ሊያስመሰግኗቸውና ሊያሸልሟቸው የሚችሉ በመሆናቸው ኮርተንባቸዋል ብለዋል።

የጠቅላይ ሚኒስትሩ ትልቅ ሽልማት የኢትዮጵያ ህዝብ አንድ መሆን ነው ያሉት ተቀዳሚ ሙፍቲ ሀጅ ኡመር በዚህም መላዉ የኢትየጵያ ህዝብ ደስ ሊለው እንደሚገባ ገልፀዋል። ተቀዳሚ ሙፍቲ ሀጅ ኡመር ኢድሪስ መልካም ተግባር መስራት ምን ያህል አስፈላጊና ተጽእኖ መፈጥር እንደሚችል ማሳያ መሆኑን የጠቅላይ ሚኒስትሩ ሽልማት ያሳያል ብለዋል።

Via FBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የጎንደር ዩንቨርሲቲ የፈረንሳይኛ ቋንቋ የስልጠና ማእከል ለመክፈት ከፈረንሳይ ኤምባሲ ጋር ስምምነት መድረሱን አስታወቀ፡፡ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ በፈረንሳይኛ ቋንቋ ተማሪዎችን በዲፕሎማ ፕሮግራም ተቀብሎ ለማሰልጠን ተቀማጭነቱ ኢትዮጵያ ውስጥ ከሆነው የፈረንሳይ ኤምባሲ ጋር ስምምነት ላይ መድረሱን ዩኒቨርስቲው አስታወቋል።

Via #ENA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#MALALA

"የ2019 #የሰላም የኖቤል ሽልማት ተሸላሚ ጠቅላይ ሚኒስተር #AbiyAhmedAli፣ እንዲሁም ለኢትዮጵያ እና ኤርትራ እርቅ እየሰራችሁ ላላችሁ ሁሉ እንኳን ደስ አላችሁ።" -- ፓኪስታናዊቷ ወጣት ማላላ የሱፍዛይ/የ2014 የኖቤል ሰላም ሽልማት አሸናፊ የ2014 የኖቤል ሰላም ሽልማት አሸናፊ/

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#UAE

የጠቅላይ ሚንስተር ዶክተር አብይ አህመድ ኖቤል ማሸነፍን የUAE ዋና ከተማ #አቡዲያቢ በፌሽታ እያከበረችው ትገኛለች። ማምሻውን #የAdnocGroup ሰማይ ጠቀስ ህንጻን ጨምሮ ሌሎች 'ላንድማርኮች' የኢትዮጵያ ሰንደቃላማ እንዲያንጸባርቁ ተደርገዋል።

Via ELU
PHOTO: SULIMAN DEDEFO

@tsegabwolde @tikvahethiopia
አቡዳቢ የሚገኘው #የAdnocGroup ሰማይ ጠቀስ ህንጻ ማምሻውን በኢትዮጵያ #ሀገራችን ሰንደቅ ዓላማ ደምቋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#UAE

በተባበሩት አረብ ኤሜሬቶች የኢትዮጵያ አምባሳደር የሆኑት ሱሌይማን ደደፎ በማህበራዊ ገጻቸው ላይ “አቡ ዳቢ የጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ የኖቤል ሽልማትን እንዲህ እያከበረች ነው” ሲሉ በኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ ቀለማት የደመቁ የአቡ ዳቢ ህንጻዎቸን የሚያሳዩ ተንቀሳቃሽ ምስሎችን ለጥፈዋል። በአንዱ ህንጻ ላይ በእንግሊዘኛ “የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አህምድ የ2019 የኖቤል የሰላም ሽልማት አሸናፊ በመሆነዎ አንኳን ደስ ያልዎ” የሚል መልዕክት ይታያል። የጠቅላይ ሚንስትር ዐብይን እና የልዑል አልጋ ወራሽ ሞሐመድ ቢን ዛይድን ምስል የሚያሳይ ፎቶግራፍም በህንጻው ላይ ይታያል።

Via BBC
ምስል፦ አምባሳደር ሱሌይማን ደደፎ

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ሼር #share

ለማሻሻያ ሥራ የሚቋረጥ የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት!

ቅዳሜ ጥቅምት 1 ቀን 2012 ዓ.ም ከጠዋቱ 2:00 ሰዓት እስከ ቀኑ 6:00 ሰዓት ድረስ፣ በእህል በረንዳ፣ በአውቶብስ ተራ፣ በአዲስ ከተማ ት/ቤት፣ በገነሜ ት/ቤት፣ በመሳለምያ፣ በእሳት አደጋ፣ በሳንባ ነቀርሳ፣ በአበበ ቢቂላ እስታድየም፣ በታይዋን፣ በሆላንድ ኤምባሲ፣ በፈረንሳይ ኤምባሲ፣ በጉራራ፣ በፊልም ማእከል፣ በራስ ካሳ ክሊኒክ፣ በአቦ ቤ/ክ፣ በእንጦጦ ኪዳነ ምህረት ቤ/ክ፣ በጎፋ ኪዳነ ምህረት፣ በመካኒሳ ቆሬ ኮንደሚኒየም፣ በቆሬ ካምፕ፣ በብስራተ ገብርኤል ፣ በፅዮን ሆቴል፣ በአዲሱ ገበያ፣ በሸጎሌ አንበሳ ሳተላይት ጋራዥ፣ በድሬ ቆዳ እና አካባቢዎቻቸው፣ በከፍተኛ የኤሌክትሪክ መስመር ላይ የማሻሻያ ሥራ ለማከናወን የኃይል አቅርቦት የሚቋረጥ በመሆኑ ክቡራን ደንበኞቻችን ከወዲሁ አስፈላጊውን ቅድመ ዝግጅት እንድታደርጉ በአክብሮት እናሳውቃለን፡፡

#የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት

@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
ቢሾፍቱ ከተማ/ኡኬ ደንካካ የሚባለው አካባቢ በደረሰው የጦር አውሮፕላን መከስከስ አደጋ የሁለት አብራሪዎች ህይወት እንዳለፈ ለጉዳዩ ቅርብ ነኝ ያሉ የቤተሰባችን አባል ከቢሾፍቱ መረጃ ሰጥተዋል። Via DIN/TIKVAH ETH FAMILY/ VIDEO: ሮብኤል/TIKVAH ETH FAMILY/ ተጨማሪ መረጃዎች ይፋ ሲደረጉ እናቀርባለን! @tsegabwolde @tikvahethiopia
#ቢሾፍቱ

በልምምድ ላይ የነበረ አንድ የኢትዮጵያ የጦር አውሮፕላን ተከስክሶ የሁለት ሰዎች ህይወት አልፏል። አውሮፕላኑ ዛሬ ጠዋት ቢሾፍቱ ከሚገኘው የአየር ሃይል ካምፕ በመነሳት በልምምድ ላይ እያለ በምስራቅ ሸዋ ዞን አደአ ወረዳ ኡኬ ደንካካ በተሰኘ ቦታ መከስከሱን የምስራቅ ሸዋ ዞን ኮሚኒኬሽን ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ አበራ ያሚ ለዶቸ ቨለ አረጋግጠዋል።

በአደጋው የሁለት አብራሪዎች ህይወት ማለፉንም አቶ አበራ ገልጸዋል። ከሟቾች መካከል የአንደኛው አስክሬን አውሮፕላኑ ከተከሰከሰበት ከ100 ሜትር በላይ ርቆ መገኘቱንም ተናግረዋል። የአደጋው መንስኤ ገና በመጣራት ላይ መሆኑንም ነው አቶ አበራ የተናገሩት።

«በደረሰን መረጃ መሰረት የተከሰከሰው አውሮፕላን የጦር መለማመጃ አውሮፕላን ነው። ሁለት ሰዎች በልምምድ ላይ እንደነበሩም ነው ያጣራነው። ከሁለቱ ሰዎች የአንደኛው አስክሬን ሲገኝ የሌላኛው ከአውሮፕላኑ ጋር ቃጠሎ ደርሶበታል። አደጋው የደረሰው ከምሳ ሰአት በፊት ሲሆን እስካሁን የአደጋው መንስኤ በመጣራት ላይ መሆኑን ነው የምናውቀው» ብለዋል።

Via #DW

PHOTO: TIKVAH-ETH

@tsegabwolde @tikvahethiopia
የዛሬው የጦር አውሮፕላን #በተከሰከሰበት በዚሁ በአደአ ወረዳ፣ ከጥቂት አመታት በፊት በጦር ሂሊኮፕተር ላይ በደረሰ ተመሳሳይ አደጋ የስድስት ሰዎች ህይወት ጠፍቷል። የ157 ሰዎችን ህይወት የቀጠፈው የመጋቢት 2011ዱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የቦይንግ 737 ማክስ 8 አውሮፕላን አደጋ የደረሰውም በዚሁ አካባቢ ነበር።

Via የጀርመን ራድዮ
PHOTO: TIKVAH ETH FAMILY

@tsegabwolde @tikvahethiopia
This media is not supported in your browser
VIEW IN TELEGRAM
UAE #አቡዳቢ በታክሲ ስራ ላይ የተሰማራ ወንድማችንና የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባል 'ማሪና ሞል' ያለውን ድባብ በቪድዮ አጋርቶናል!!!
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Dubai በዱባይ የሚገኘው ሰማይ ጠቀሱ 'ቡርጂ ከሊፋ' ህንፃ የጠ/ሚ ዶ/ር ዐብይ አህመድን የኖቤል የሰላም ሽልማት ማሸነፍን አስመልክቶ ከላይ በምታዩት መልኩ ህንፃው ተውቧል! ፎቶውን ያጋራን በአሁን ሰዓት ዱባይ የሚገኝ የTIKVAH-ETH ቤተሰብ አባል ነው።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#NobelPeacePrize

ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ "የኖቤል የሰላም ሽልማት" በማሸነፋቸው የሀገራችንን ስም በዓለም መድረክ ከማስጠራት ባለፈ 918,000 የአሜሪካ ዶላር በገንዘብ፣ የወርቅ ሜዳልያ እንዲሁም ዲፕሎማ ይሸለማሉ!!

#TIKVAH_ETHIOPIA
@tsegabwolde @tikvahethiopia