#ALGERIA
አልጄሪያውያን በመጪው የፈረንጆቹ ታህሳስ 12 ቀን 2019 የሀገራቸውን ፕሬዚዳንት እንደሚመርጡ ታውቋል። ምርጫ የሚካሄድበት ቀን በጊዜያዊ የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት አብደልቃድር ቤንሳላ ይፋ ተደርጓል። የአልጄሪያ ወታደራዊ አዛዥ ጀኔራል አህመድ ጋይድ ሳላህ ሀገሪቱ ምርጫ የምታካሂድበት ጊዜ በይፋ እንዲነገር ከሳምንታት በፊት ትዕዛዝ መስጠታቸው ይታወሳል። ፕሬዚዳንታዊ ምርጫው ለሃምሌ 4 ታቅዶ የነበረ ቢሆንም እጩዎች ባለመቅረባቸው ምክንያት መራዘሙ ይታወሳል። ሀገሪቱን ለ20 ዓመታት የመሯት የ82 ዓመቱ አብደልአዚዝ ቡተፍሊካ ህዝባዊ ጫናው ሲበረታባቸው ባለፈው ሚያዚያ ላይ ስልጣን ለቀዋል።
Via #BBC/ENA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አልጄሪያውያን በመጪው የፈረንጆቹ ታህሳስ 12 ቀን 2019 የሀገራቸውን ፕሬዚዳንት እንደሚመርጡ ታውቋል። ምርጫ የሚካሄድበት ቀን በጊዜያዊ የሀገሪቱ ፕሬዚዳንት አብደልቃድር ቤንሳላ ይፋ ተደርጓል። የአልጄሪያ ወታደራዊ አዛዥ ጀኔራል አህመድ ጋይድ ሳላህ ሀገሪቱ ምርጫ የምታካሂድበት ጊዜ በይፋ እንዲነገር ከሳምንታት በፊት ትዕዛዝ መስጠታቸው ይታወሳል። ፕሬዚዳንታዊ ምርጫው ለሃምሌ 4 ታቅዶ የነበረ ቢሆንም እጩዎች ባለመቅረባቸው ምክንያት መራዘሙ ይታወሳል። ሀገሪቱን ለ20 ዓመታት የመሯት የ82 ዓመቱ አብደልአዚዝ ቡተፍሊካ ህዝባዊ ጫናው ሲበረታባቸው ባለፈው ሚያዚያ ላይ ስልጣን ለቀዋል።
Via #BBC/ENA
@tsegabwolde @tikvahethiopia