TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.4K photos
1.51K videos
215 files
4.12K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የገቢዎች ሚኒስቴር🔝

በያዝነው ሳምንት በተለያዩ የመቆጣጠሪያ ጣቢዎች በድምሩ 4,480,305 ብር የሚገመት የኮንትሮባድ ዕቃ በቁጥጥር ስር ውሏል፡፡

#ቡሌ_ሆራ የመቆጣሪያ ጣቢያ ላይ 627,100 ብር የሚገመት ተንቀሳቃሽ ስልኮች፣ ቻርጀሮች እና ጀነሬተሮች የሚያካትት የኮንትሮባንድ ዕቃ መጋቢት 9/2011 ዓ.ም በቁጥጥር ስር ዋለ፡፡ የኮንትሮባንድ ዕቃው በሰሌዳ ቁጥር ኮድ3-94467 አ.አ በሆነ ተሸከርካሪ ሲጓጓዝ በኦሮሚያ ፖሊስና በጉምሩክ ሰራተኞች ትብብር በቁጥጥር ስር ውሏል፡፡

#በምስራቅ_ሀረርጌ_ዞን ኮምቦልቻ ከተማ አካባቢ የሰሌዳ ቁጥር ኮድ3-19171 አ.አ FSR ተሸከርካሪ 697,300 ብር ግምታዊ ዋጋው ኮንትሮባንድ የሆነ ኤሌክትሮኒክስ፣ መለዋወጫ እና ፌሮ ብረት በኦሮሚያ አድማ ብተና ፖሊስ፣ በመከላከያ ሰራዊት እና በጉምሩክ ሰራተኞች መጋቢት 9/2011 ዓ.ም በቁጥጥር ስር ውሏል ግምታዊ ዋጋ 1,200,000 ብር የሆነ መድሃኒት፣ አልባሳት፣ የቤት ክዳን ቆርቆሮ ፣ ስኳር እና ሌሎች የኮንትሮባንድ ዕቃዎች መጋቢት 10 ቀን 2011 ዓ.ም ከምሽቱ 5፡00 ላይ የሰሌዳ ቁጥር 01526 ሱማ እና 02621 ሱማ በሆኑ ተሸከርካሪዎች ወደ ጅግጅጋ ለማስገባት ሲሞከር በአድማ ብተና አባላት እና በጉምሩክ ሰራተኞች ተይዟል፡፡

በደቡብ ክልል ገደብ፣ ወናጎ እና አርባ ምንጭ ከተሞች 2,026,105 ብር የሚገመት መድሃኒት፣ አልባሳት እና ሌሎች የኮንትሮባንድ ዕቃዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡

ምንጭ፦ ገቢዎች ሚኒስቴር
@tsegabwolde @tikvahethiopia