አሳዛኝ ዜና‼️
በምሥራቅ ጎጃም ዞን ደብረ ማርቆስ ከተማ ቀበሌ 07 ልዩ ስሙ ጨሞጋ አውራ ጎዳና ዛሬ ከረፋዱ 3:00 አካባቢ በደረሰ #የተሽከርካሪ_መገልበጥ አደጋ 16 ሰዎች ጉዳት ደርሶባቸዋል፡፡
ከደብረ ማርቆስ ወደ የጁቤ በመሄድ ላይ የነበረ የሕዝብ ማመላለሻ መኪና ተገልብጦ ነው አደጋው የደረሰው፡፡
በአደጋው ጉዳት የደረሰባቸው 16 ሰዎች በደብረማርቆስ ሪፈራል ሆስፒታል የሕክምና ዕርዳታ እየተደረገላቸው ነው፡፡
አደጋው የተከሰተው በፍጥነት በማሽከርከር መሆኑም ታውቋል፤ የመገልበጥ አደጋ ያደረሰው አሽከርካሪ ደግሞ ለጊዜው ተሰውሯል፡፡
#ተጠርጣሪውን በቁጥጥር ስር ለማዋል ፖሊስ ጥረት እያደረገ መሆኑን የምሥራቅ ጎጃም ዞን ፖሊስ መምሪያ የሕዝብ ግንኙነት አስተባባሪ ኢንስፔክተር ጎበዜ ይርሳው ተናግረዋል፡፡
ምንጭ፦ አብመድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በምሥራቅ ጎጃም ዞን ደብረ ማርቆስ ከተማ ቀበሌ 07 ልዩ ስሙ ጨሞጋ አውራ ጎዳና ዛሬ ከረፋዱ 3:00 አካባቢ በደረሰ #የተሽከርካሪ_መገልበጥ አደጋ 16 ሰዎች ጉዳት ደርሶባቸዋል፡፡
ከደብረ ማርቆስ ወደ የጁቤ በመሄድ ላይ የነበረ የሕዝብ ማመላለሻ መኪና ተገልብጦ ነው አደጋው የደረሰው፡፡
በአደጋው ጉዳት የደረሰባቸው 16 ሰዎች በደብረማርቆስ ሪፈራል ሆስፒታል የሕክምና ዕርዳታ እየተደረገላቸው ነው፡፡
አደጋው የተከሰተው በፍጥነት በማሽከርከር መሆኑም ታውቋል፤ የመገልበጥ አደጋ ያደረሰው አሽከርካሪ ደግሞ ለጊዜው ተሰውሯል፡፡
#ተጠርጣሪውን በቁጥጥር ስር ለማዋል ፖሊስ ጥረት እያደረገ መሆኑን የምሥራቅ ጎጃም ዞን ፖሊስ መምሪያ የሕዝብ ግንኙነት አስተባባሪ ኢንስፔክተር ጎበዜ ይርሳው ተናግረዋል፡፡
ምንጭ፦ አብመድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia