TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.4K photos
1.51K videos
215 files
4.12K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ወንጀል ነክ መረጃ‼️

ከባድ የአካል ጉዳት ያደረሰዉ #ተከሳሽ በእስራት ተቀጣ፡፡ ተከሳሽ #ሳሙኤል_ጎችል_ወልደመስቀል በ1996 ዓ.ም የወጣዉን የኢፌዴሪ የወንጀል ህግ አንቀፅ 555/ለ ስር የተመለከተዉን ድንጋጌ ተላልፎ በፈፀመዉ ከባድ የአካል ጉዳት ማድረስ ወንጀል ተከሷል፡፡

ተከሳሽ በሌላ ሰዉ አካል ላይ ጉዳት ለማድረስ በማሰብ ሰኔ 2 ቀን 2010 ዓ.ም በግምት ከምሽቱ 12፤30 ሲሆን በየካ ክፍለ ከተማ ወረዳ 5 ልዩ ቦታዉ በግ ተራ ተብሎ ከሚጠራዉ አካባቢ የግል ተበዳይ አብርሀም ታፈረን በቦክስ በመምታት የላይኛዉ የፊት ለፊት አራት ጥርሶቹ እንዲወልቁ ያደረገ በመሆኑ በፈፀመዉ ከባድ የአካል ጉዳት ማድረስ ወንጀል ነዉ፡፡

ተከሳሽ ከላይ በክስ ዝርዝሩ አደረክ የተባልኩትን ድርጊት አልፈፀምኩም ሲል የእምነት ክህደት ቃሉን ቢሰጥም ዐቃቢ ህግ 4 የሰዉ ምስክሮችንና የሰነድ የማስረጃዎቹን አጠናቅሮ ለፍርድ ቤቱ አቅርቧል፡፡

መዝገቡን የተመለከተዉ በፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት የየካ ምድብ የወንጀል ችሎትም ተከሳሽ ጥፋተኛ ነዉ ሲል ታህሳስ 08 ቀን 2011 ዓ.ም በዋለዉ 3ተኛ ወንጀል ችሎት በቅጣት ዉሳኔው ተከሳሽን ያርማል ሌሎችንም ያስተምራል በማለት በ2 አመት ከ9 ወር እስራት እንዲቀጣ ወስኖበታል፡፡

ምንጭ፦ የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ
@tsegabwolde @tikvahethiopia