TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.4K photos
1.51K videos
215 files
4.12K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update ዛሬ በኦሮሚያ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች የተቃውሞ ሰልፎች ዛሬ ህዳር 25/03/2011 ዓ.ም. ተድርገዋል።

ፎቶ፦ elu
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጠገዴ  ወረዳ‼️

በማዕከላዊ ጎንደር ዞን ጠገዴ ወረዳ  ተቀብሮ የነበረ #የእጅ_ቦምብ ፈንድቶ የሁለት ህፃናት ህይወት  ሲያልፍ በስድስቱ ላይ የመቁሰል አደጋ መድረሱን ፓሊስ አስታወቀ።

የዞኑ ፓሊስ መመሪያ ሀላፊ ኮማንደር #እንየው_ዘውዴ፥ ቦምቡ በጠገዴ ወረዳ ቡሬ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት አቅራቢያ በግምት በ350 ሜትር ርቀት የተከሰተ ነው ብለዋል።

ሀላፊው ኤፍ 1 የተባለ የእጅ ቦንብ ህፃናት ተማሪዎች ዋርካ ስር ሆነው እያነበቡ በነበረበት ወቅት መፈንዳቱንና ጉዳት ማድረሱን ተናግረዋል።

በፍንዳታው ስምንት ህፃናት የመቁሰል አደጋ እንዳጋጥሟቸውና  ሁለቱ ሆስፒታል እንደደረሱ ህይወታቸው እንዳለፈ ገልፀዋል።

ፈንድቶ ጉዳት ያደረሰው ቦንቡ መሬት ውስጥ ተቀብሮ መቆየቱን ኮማንደሩ ተናግረዋል።

ምንጭ፦ ፋና ብሮድካስቲንግ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ከወለጋ ዩኒቨርሲቲ🔝

"በአሁኑ ሰአት በወለጋ ዩኒቨርስቲ ማለትም ከ5:30-7:30 በጣም አለመረጋጋት አለ እንዳውም ብሎክ 714 እና 722 ሁለት ተማሪዎችተመተው ነቀምቴ ሪፈራል ሆስፒታል ሄደዋል ነው። ግቢው እንዳለ በክልል ፖሊሶች ተከቧል ተማሪዎችም ወደ ጫካ እየገቡ ነው። እኛም በጣም ፈርተን ዶርም ተቀምጠናል። አብዛኛው ተማሪም እያለቀሱ ይገኛሉ በጣም የሚያሳዝን ሁኔታ ነው። ካፌ ውስጥም በመግባት ተማሪዎችን ደብድበዋል።"

@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Update የሴኔጋሉ ተወካይ የአውሮፓዊያኑ 2019 የመንግስታቱ ድርጅት የሰብዓዊ መብት ምክር ቤት ፕሬዝዳንት ሆነው ተመረጡ፡፡ ኮሊ ሴክ የተባሉት እኚ በድርጅቱ የሀገረ ሴኔጋል ተወካይ ፕሬዝዳንት ሆነው ሲያገለግሉም ሁለት ምክትል ፕሬዝዳንቶች እንደሚኖሯቸው ተነግሯል፡፡

@tsegabwolde @tikahethiopia
ነቀምት‼️

ዛሬ በነቀምቴ ከተማ የቴሌኮም አገልግሎት መቋረጡ ኢትዮ ቴሌኮም ተናግሯል፡፡ ከማለዳው 12፡45 ጀምሮ አገልግሎቱ መቋረጡ ታውቋል፡፡

ለነቀምቴ ከተማም የቴሌኮም አገልግሎት የሚሰጠው የኮር ሳይት በኤሌክትሪክ ሀይል መቋረጥ ምክንያት አገልግሎት መስጠት እንዳልተቻለ ተሰምቷል፡፡

በኦሮሚያ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት ነቀምት ከተማ የተቋረጠውን አገልግሎት መላ ለመስጠትም ኢትዮ ቴሌኮም በስፍራው ባለሙያዎችን ልኳል፡፡ ለዚህም ህዝቡን #ይቅርታ ጠይቋል፡፡

ምንጭ፦ ሸገር 102.1
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ወለጋ ዩኒቨርሲቲ🔝በተቋሙ ውስጥ ተፈጥሮ የነበረው አለመረጋጋት አሁን መረጋጋቱን እና ግቢው ወደሰላማዊ እንቅስቃሴ እየተመለሰ እንደሆነ በግቢው ውስጥ የሚገኙ ተማሪዎች ለTIKVAH-ETH ባደረሱት መልዕክት አሳውቀዋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሀሰተኛ መረጃ🔝

ፌክ ፖስት: "ከፊንፊኔ ወደ #መቀሌ ሊገባ ሲል የተያዘ"

ጉግል: "የዚምባብዌ ፋይናንስ ሚኒስትር ቤት ውስጥ የተገኘ 10 ሚልዮን ዶላር"

ምንጭ፦ ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ‼️

የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ ትምህርት ሚኒስቴር የማያውቀው የትምህርት ክፍል አለ በሚል በማህበራዊ ትስስር ድረ ገጾች የተሰራጨውን መረጃ #አስተባበለ

በማህበራዊ ትስስር ድረ ገጾች በቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩቱ ስር ዩኒቨርሲቲውና ትምህርት ሚኒስቴር የማያውቀው የትምህርት ክፍል ተገኝቷል የሚል መረጃ ተለቋል።

የዩኒቨርሲቲው የአካዳሚክ ምክትል ፕሬዚዳንት ዶክተር #የቻለ ዩኒቨርሲቲው ማንኛውንም የትምህርት ክፍል የሚከፈተው ሁሉም ባለድርሻ አካላት ተወያይቶበት፣ ማኔጅመንቱና ቦርዱ  አጽድቆት  እና ከትምህርት ሚኒስቴር ፍቃድ ሲያገኝ ብቻ ነው መሆኑን ለfbc ተናግረዋል።

ሁሉም የትምህርት ክፍሎች በዚህ መሰረት የተከፈቱ መሆኑን  የገለፁት ዶክተር የቻለ፥ የፕሮዳክሽን ኢንጂነሪንግ ትምህርት ክፍልም በዚሁ መሰረት የተከፈተ መሆኑን አስታውቀዋል።

ሜታል ፕሮዳክሽን ኢንጂነሪንግ የሚል ስያሜ እንደተሰጠውና ይህም ተማሪዎች በልምምድና የተግባር ትምህርት ወቅት በብሄራዊ ብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን(ሜቴክ) እድሉን እንዲያገኙ ለማድረግ ነው ብለዋል።

ይህም ተቋሙ ከትምህረት ክፍሉ ጋር በብዙ የሚያገናኘው የስራ አይነት ያለው በመሆኑ ስያሜው በዛ እንዲሰየም መደረጉን ተናግረዋል።

ነገር ግን ይህ ትምህርት ሚኒስቴር ከሚያውቀው ውጪ ስያሜ ስለሚሆን ወደ ትክክለኛው ስያሜ መመለስ አለበት በሚል ውሳኔ ላይ መደረሱን አብራርተዋል።

በዚህም በዩኒቨርሲቲው ሜታል ፕሮዳክሽን ኢንጂነሪንግ የሚለው ስያሜ ቀርቶ ፕሮዳክሽን ኢንጂነሪንግ እንዲሆን ተወስኗል።

ምንጭ፦ fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Update ግጭት በተከሰተባቸው አካባቢዎች እጃቸውን ያስገቡ አካላትን የሚለይ የምርመራ ቡድን ችግሩ ወደ ተከሰተባቸው ሰፍራዎች መላኩን ጠቅላይ አቃቤ ህግ አስታወቀ። ጠቅላይ ዓቃቤ ህግ በቀጣይም የተገኙ ዉጤቶችን ለሕዝብ እንደሚያሳውቅ ገልጿል፡፡

@Tsegabwolde @tikvahethiopia
ጭልጋ ወረዳ‼️

‹‹በጭልጋ አካባቢ አንድ ሰው ተገድሏል፤ 39 ቤቶች ተቃጥለዋል፤ 50 ቤቶችና 9 ወፍጮ ቤቶች ተዘርፈዋል››

‹‹ከጥቃቱ ጋር በተያያዘ 153 ሰዎች በተጠርጣሪነት በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡›› የማዕከላዊ ጎንደር ዋና አስተዳዳሪ
.
.
በማዕከላዊ ጎንደር ዞን ጭልጋ አካባቢ ‹‹በቅማንት ብሔር ስም በህቡዕ ተደራጅተው የሚነግዱ›› የተባሉ ቡድኖች ትናንት ጥቃት አድርሰዋል፡፡ በጥቃቱ ‹‹የአንድ ሰው ሕይወት አልፏል፤39 ቤቶች ተቃጥለዋል፤ 50 ቤቶችና 9
ወፍጮ ቤቶች ተዘርፈዋል›› ብለዋል የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ #ብርሃኑ_ጣምያለው፡፡

አቶ ብርሃኑ እንዳሉት ሌሎች 8 ሰዎችም ቆስለዋል፡፡ ከጥቃቱ ጋር በተያያዘ 153 ሰዎች በተጠርጣሪነት መለየታቸውንና ወደ ሕግ ለማቅረብ እንደሚሠራም ዋና አስተዳዳሪው ገልጸዋል፡፡

አካባቢው ወደ ከፋ ግጭት እንዳያመራ የክልሉ የፀጥታ ኃይሎች ከፌዴራል ፖሊስና ከመከላከያ ሠራዊት ጋር በመቀናጀት አካባቢውን የማረጋጋት ሥራ እያከናወኑ መሆናቸውንም አቶ ብርሃኑ አብራርተዋል፡፡

ግጭቱን ዘገባው በተጠናቀረበት ወቅት ማስቆም የተቻለ ሲሆን ሙሉ በሙሉ የአካባቢውን ሰላም ወደ ቀደመ ሁኔታ ለመመለስ መስተዳድሩ ከሀገር ሽግሌዎችና ከሃይማኖት አባቶች ጋር አብሮ እየሠራ መሆኑንም አስታውቀዋል፡፡

ኅብረተሰቡ የአካባቢውን ሰላምና ደኅንነት ለማደፍረስ የሚጥሩ ኃይሎችን አጥብቆ እንዲያወግዛቸውና ሕግ ፊትም ለማቅረብ በሚደረገው ጥረት ከመንግሥት ጋር በመሆን የበኩሉን ኃላፊነት እንዲወጣ ዋና አስተዳዳሪው ጥሪ አስተላልፈዋል፡፡አሁን ላይ አካባቢው በመረጋጋት ላይ እንደሆነ ከዞኑ የተገኘው መረጃ ያሳያል፡፡

ምንጭ፦ አብመድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia