አዲሱ ካቢኔት‼️
ጠ/ሚ ዶክተር #አብይ_አህመድ በአፍሪካ የመጀመሪያ የሆነውን 50% በሴቶች የተዋቀረ ካቢኔት ዛሬ ለስራ አስፈፃሚ አቅርበው #አፀድቀዋል።
#TIKVAHETHIOPIA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጠ/ሚ ዶክተር #አብይ_አህመድ በአፍሪካ የመጀመሪያ የሆነውን 50% በሴቶች የተዋቀረ ካቢኔት ዛሬ ለስራ አስፈፃሚ አቅርበው #አፀድቀዋል።
#TIKVAHETHIOPIA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የአዲሱ ካቢኔ #ግምት በጥቂቱ‼️
በአዲሱ ካቢኔ ውስጥ የተካተቱ ናቸው ተብሎ የደረሰኝ መረጃ፦
🔹ወ/ሮ ሙፈሪያት - የሰላም ሚኒስትር
🔹ወ/ሮ ፈትለወርቅ - የንግድ እና ኢንድስትሪ ሚኒስትር
🔹ኢንጂነር አይሻ - የባህል እና ቱሪዝም ሚኒስትር
🔹ዶክተር ኢርጎጌ - የሰራተኛ እና ማህበራዊ ሚኒስትር
🔹ወ/ሮ አዳነች አቤቤ - የትራንስፖርት ሚኒስትር
🔹ዶክተር ሂሩት - የከፍተኛ ትምህርት እና የሳይንስ ሚኒስትር
🔹ወ/ሮ ዳግማዊት ደግሞ__________
.
.
ሌሎችም ያልተጠበቁ ሹመቶች ይኖራሉ ተብሎ #ይጠበቃል። የካቢኔ አባላት ቁጥር ከ28 ወደ 20 ይቀንሳል።
🔹ነገ ጥዋት ተጨማሪ የሚደርሱኝን የስም ዝርዝሮች የማቀርብ ይሆናል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በአዲሱ ካቢኔ ውስጥ የተካተቱ ናቸው ተብሎ የደረሰኝ መረጃ፦
🔹ወ/ሮ ሙፈሪያት - የሰላም ሚኒስትር
🔹ወ/ሮ ፈትለወርቅ - የንግድ እና ኢንድስትሪ ሚኒስትር
🔹ኢንጂነር አይሻ - የባህል እና ቱሪዝም ሚኒስትር
🔹ዶክተር ኢርጎጌ - የሰራተኛ እና ማህበራዊ ሚኒስትር
🔹ወ/ሮ አዳነች አቤቤ - የትራንስፖርት ሚኒስትር
🔹ዶክተር ሂሩት - የከፍተኛ ትምህርት እና የሳይንስ ሚኒስትር
🔹ወ/ሮ ዳግማዊት ደግሞ__________
.
.
ሌሎችም ያልተጠበቁ ሹመቶች ይኖራሉ ተብሎ #ይጠበቃል። የካቢኔ አባላት ቁጥር ከ28 ወደ 20 ይቀንሳል።
🔹ነገ ጥዋት ተጨማሪ የሚደርሱኝን የስም ዝርዝሮች የማቀርብ ይሆናል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ እጩ የካቢኔ አባላትን ለምክር ቤቱ በማቅረብ ላይ ይገኛሉ።
አዲሱ የካቢኔ አባላትም በብቃት፣ በልምድ፣ በትምህርት ዝግጅት እና ለውጥን መምራት የሚችሉ ተብለው የተመረጡ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ለምክር ቤቱ አብራርተዋል።
እንዲሁም አዲሱ ካቢኔ በኢትዮጵያ ብሎም በአፍሪካ ለመጀመሪያ በሚባል ደረጃ 50 በመቶ ሴቶች ናቸው የተባለ ሲሆን፥ ይህም ከ20 የካቢኔ አባላት 10ሩ ሴቶች መሆናቸውን አስረድተዋል።
በዚህም መሰረት፦
1. ወይዘሮ ሙፈሪያት ካሚል- የሰላም ሚኒስትር
2. ወይዘሮ ፈትለወርቅ ገብረእግዚአብሄር- ንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስትር
3. ኢንጂነር አይሻ መሃመድ- የሀገር መከላከያ ሚኒስትር
4. አቶ አህመድ ሽዴ- የገንዘብና ኢኮኖሚ ሚኒስትር
5. አቶ ኡመር ሁሄን- የግብርና ሚኒስትር
6. ወይዘሮ አዳነች አቤቤ- የገቢዎች ሚኒስትር
7. ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ- የሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር
8. ዶክተር ፍፁም አሰፋ- የፕላንና ልማት ኮሚሽን ሚኒስትር
9. ዶክተር ሂሩት ወልደማርያም- የሳይንስና ከፍተኛ ትምህረት ሚኒስትር
10. ዶክተር ጥላዬ ጌቴ- የትምህርት ሚኒስትር
11. ወይዘሪት የዓለምፀጋይ አሰፋ- የሴቶች ህጻናትና ወጣቶች ሚኒስትር
12. ወይዘሮ ዳግማዊት ሞገስ- የትራንስፖርት ሚኒስትር
13. ዶክተር ጌታሁን መኩሪያ - የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር
14. አቶ ጃንጥራር አባይ-የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስትር
15. ዶክተር ሳሙኤል ሁርካቶ- የማዕድንና ነዳጅ ሚኒስትር
16. ዶክተር ሂሩት ካሳው-የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትር
ምንጭ፦ ፋና ብሮድካስቲንግ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አዲሱ የካቢኔ አባላትም በብቃት፣ በልምድ፣ በትምህርት ዝግጅት እና ለውጥን መምራት የሚችሉ ተብለው የተመረጡ መሆኑን ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ለምክር ቤቱ አብራርተዋል።
እንዲሁም አዲሱ ካቢኔ በኢትዮጵያ ብሎም በአፍሪካ ለመጀመሪያ በሚባል ደረጃ 50 በመቶ ሴቶች ናቸው የተባለ ሲሆን፥ ይህም ከ20 የካቢኔ አባላት 10ሩ ሴቶች መሆናቸውን አስረድተዋል።
በዚህም መሰረት፦
1. ወይዘሮ ሙፈሪያት ካሚል- የሰላም ሚኒስትር
2. ወይዘሮ ፈትለወርቅ ገብረእግዚአብሄር- ንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስትር
3. ኢንጂነር አይሻ መሃመድ- የሀገር መከላከያ ሚኒስትር
4. አቶ አህመድ ሽዴ- የገንዘብና ኢኮኖሚ ሚኒስትር
5. አቶ ኡመር ሁሄን- የግብርና ሚኒስትር
6. ወይዘሮ አዳነች አቤቤ- የገቢዎች ሚኒስትር
7. ዶክተር ኤርጎጌ ተስፋዬ- የሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር
8. ዶክተር ፍፁም አሰፋ- የፕላንና ልማት ኮሚሽን ሚኒስትር
9. ዶክተር ሂሩት ወልደማርያም- የሳይንስና ከፍተኛ ትምህረት ሚኒስትር
10. ዶክተር ጥላዬ ጌቴ- የትምህርት ሚኒስትር
11. ወይዘሪት የዓለምፀጋይ አሰፋ- የሴቶች ህጻናትና ወጣቶች ሚኒስትር
12. ወይዘሮ ዳግማዊት ሞገስ- የትራንስፖርት ሚኒስትር
13. ዶክተር ጌታሁን መኩሪያ - የኢኖቬሽን እና ቴክኖሎጂ ሚኒስትር
14. አቶ ጃንጥራር አባይ-የከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስትር
15. ዶክተር ሳሙኤል ሁርካቶ- የማዕድንና ነዳጅ ሚኒስትር
16. ዶክተር ሂሩት ካሳው-የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትር
ምንጭ፦ ፋና ብሮድካስቲንግ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሰበር ዜና‼️የህዝብ የወካዮች ምክረ ቤት አፈ ጉባዔ ወይዘሮ #ሙፈሪያት_ካሚል የስራ መልቀቂያ አቀረቡ። ወይዘሮ ሙፈሪያት ካሚል መልቀቂያቸውን በዛሬው እለት እየተካሄደ ባለው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 2ኛ መደበኛ ስብሰባ ላይ ነው ያቀረቡት።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ሰበር ዜና‼️ የጠ/ሚ ዶክተር #አብይ_አህመድ በአፍሪካ የመጀመሪያ የሆነውን 50 % በሴቶች የተዋቀረ ካቢኔ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በሙሉ ድምፅ #ፀድቋል።
#TIKVAHETHIOPIA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#TIKVAHETHIOPIA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የአዲስ አበባ ወጣቶች ከጦላይ እዲለቀቁ የ3 ቀን የማህበራዊ ሚዲያ ዘመቻ እየተካሄደ ይታወቃል። ዘመቻው ዛሬ ለሁለተኛ ቀን ቀጥሏል። ባለፈው ሳምንት የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር #ዘይኑ_ጀማል ጦላይ የተላኩት ወጣቶች "እያሰለጠናቸው" እንገኛለን በቀናት ውስጥ ይፈታሉ ብለው ለሚዲያ ተናግረው ነበር። ወጣቶቹ እስካሁኗ ሰዓት ድረስ ከጦላይ እንዳልተለቀቁ ለማወቅ ተችሏል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update ኢንጂነር አይሻ⬇️
ኢትዮጵያ የመጀመሪያዋን ሴት የአገር መከላከያ ሚኒስትር ሾመች። ኢንጂነር #አይሻ_መሃመድ በኢትዮጵያ ታሪክ የመጀመሪያዋ የአገር መከላከያ ሚኒስትር ሆነው ተሹመዋል።
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው መደበኛ ሰብሰባ ኢንጂነር አይሻ መሃመድን #የአገር_የመከላከያ_ሚኒስትር አድርጓቸዋል።
ኢንጂነር አይሻ የአፋር ክልል ተወላጅ ሲሆኑ የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን በሲቪል ኢንጂነሪንግ፣ ሁለተኛ ዲግሪያቸውን ደግሞ በትራንስፎርሜሽናል ሊደር ሺፕ ኤንድ ቼንጅ አግኝተዋል።
በአፋር ክልል የአደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ቢሮ ሃላፊ በመሆን ያገለገሉ ሲሆን የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትርም ነበሩ። በአሁኑ ወቅትም የኮንስትራክሽን ሚኒስትር ሆነው በማገልገል ላይ ነበሩ።
በዛሬው የምክር ቤቱ መደበኛ ስብሰባም የመጀመሪያዋ የኢትዮጵያ ሴት የአገር መከላከያ ሚኒስትር ሆነው ተሹመዋል።
ዛሬ በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ከተሾሙት 20 የካቢኔ አባላት መካከል አስሩ ሴቶች ናቸው።
ምንጭ፦ መንግስት ኮሚኒኬሽን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ኢትዮጵያ የመጀመሪያዋን ሴት የአገር መከላከያ ሚኒስትር ሾመች። ኢንጂነር #አይሻ_መሃመድ በኢትዮጵያ ታሪክ የመጀመሪያዋ የአገር መከላከያ ሚኒስትር ሆነው ተሹመዋል።
የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዛሬ ባካሄደው መደበኛ ሰብሰባ ኢንጂነር አይሻ መሃመድን #የአገር_የመከላከያ_ሚኒስትር አድርጓቸዋል።
ኢንጂነር አይሻ የአፋር ክልል ተወላጅ ሲሆኑ የመጀመሪያ ዲግሪያቸውን በሲቪል ኢንጂነሪንግ፣ ሁለተኛ ዲግሪያቸውን ደግሞ በትራንስፎርሜሽናል ሊደር ሺፕ ኤንድ ቼንጅ አግኝተዋል።
በአፋር ክልል የአደጋ መከላከልና ምግብ ዋስትና ቢሮ ሃላፊ በመሆን ያገለገሉ ሲሆን የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትርም ነበሩ። በአሁኑ ወቅትም የኮንስትራክሽን ሚኒስትር ሆነው በማገልገል ላይ ነበሩ።
በዛሬው የምክር ቤቱ መደበኛ ስብሰባም የመጀመሪያዋ የኢትዮጵያ ሴት የአገር መከላከያ ሚኒስትር ሆነው ተሹመዋል።
ዛሬ በጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ከተሾሙት 20 የካቢኔ አባላት መካከል አስሩ ሴቶች ናቸው።
ምንጭ፦ መንግስት ኮሚኒኬሽን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በዚህ ሳምንት ይለቀቃሉ‼️የአዲስ አበባ #ወጣቶች በሳምንቱ መጨረሻ እንደሚለቀቁ አዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ወጣቶቹ በዚህ ሳምንት ይለቀቃሉ‼️
ከአዲስ አበባ ተወስደው ጦላይ ወታደራዊ ማሰልጠኛ የሚገኙ የአዲስ አበባ ወጣቶች በሳምንቱ መጨረሻ እንደሚለቀቁ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ብርጋዲየር ጄኔራል #ደግፌ_በዲ ለቢቢሲ ገለፁ።
ወጣቶቹ የተያዙት "በጎዳና ላይ ንብረት ሲያወድሙና ሁከት ሲፈጥሩ ነው" ያሉት ኮሚሽነሩ መጀመሪያ ከተያዙት ተጣርቶ አሁን በማሰልጠኛ ያሉት 1174 እንደሆኑ ገልፀዋል።
እሳቸው እንደሚሉት የፈፀሙት ተግባር በህግ የሚያስጠይቃቸው ቢሆንም መታነፅ እንዳለባቸው በማመን ለዚህም ከቤተሰብና ከማህበረሰብ ቀጥሎ ሃላፊነት ያለበት መንግስት በመሆኑ ይህን ተግባሩን እየተወጣ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
"ማነፅ ብቻ ሳይሆን የወጣቶቹን ማንነት በመገንዘብ ስራ የሌለው ስራ እንዲሰራ፣ ተማሪውም ትምህርቱን እንዲቀጥል ሁኔታዎችን ለማመቻቸት ነው እነዚህ ልጆች ላይ ስራ እየሰራን ያለነው"ብለዋል ኮሚሽነሩ።
ይህን ለማድረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርን ጨምሮ የሚመለከታቸው ትብብር ላይ መሆናቸውንም ገልፀዋል።
የአዲስ አበባ ፖሊሶች ወጣቶችን በቡድን ሲደበድቡ የሚያሳይ ቪዲዮ ስለመለቀቁ ለኮሚሽነሩ ከBBC ጥያቄ ተነስቶላቸው ነበር።
ምንም እንኳ እሳቸው ተንቀሳቃሽ ምስሉን ባይመለከቱትም ቦታው ተገልፆ ትክክለኛ መረጃ ከደረሳቸው ተግባሩን በፈፀሙት አካላት ላይ ተጣርቶ #እርምጃ እንደሚወሰድ ገልፀዋል።
መሳለሚያ ሞቢል አካባቢ ለግንቦት ሰባት መሪዎች አቀባበል ሲደረግ ሰንደቅ አላማ በመስቀልና ባነሮችን በመለጠፍ ይንቀሳቀስ ነበር።
ያሳደጉትና የክርስትና ልጃቸው በአመፅ ሳይሆን የግንቦት ሰባት መሪዎች አቀባበል ላይ ባደረገው ተሳትፎ ከዚያም የቡራዮውን ግድያ በመቃወም ሰላማዊ ሰልፍ በመውጣቱ መታሰሩን አቶ ዘመነ ሞላ ለቢቢሲ ይገልፃሉ።
ከዚህ ውጭ ልጃቸው ሰላማዊ እንደሆነም ያስረዳሉ። ያሳደጉት ልጃቸው ወጣት ፍስሃ ደምስ የ25 ዓመት ወጣት ሲሆን እናቱ እንደሌለችና የሚኖረው ከአቅመ ደካማ አያቱ ጋር እንደነበር አቶ
ዘመነ ይናገራሉ።
እሳቸው እንደገለፁት የታሰረው ወደ ቤቱ የሚወስድ መንገድ ላይ አመሻሽ ላይ ነው። መጀመሪያ ወደ ተወሰደበት ፖሊስ ጣቢያ ሄደው ሲጠይቁ ጦላይ መወሰዱን መስማታቸውንና ከዚያ በኋላ ያለ ምንም መረጃ ቤተሰብ ስቃይ ላይ እንዳለ ይገልፃሉ።
የአዲስ አበባ ወጣቶች ጅምላ የመገናኛ ብዙሃንና የማህበራዊ ሚዲያ ርእሰ ጉዳይ ሆኖ ሰንብቷል። በማህበራዊ ሚዲያው የአዲስ አበባ ወጣቶች ይፈቱ የሚል ዘመቻም በመካሄድ ላይ ነው።
አምነስቲ ኢንተርናሽናል የአዲስ አበባ ወጣቶችን በጅምላ አስሮ ስልጠና ማስገባት የህግ አግባብነት እንደሌለው ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።
የህግ ባለሙያና የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ፕሮጀክት ፕሮጀክት አስተባባሪ የሆነችው ሶሊያና ሽመልስ መንግስት እነዚህን ወታደሮች አስሮ ወደ ጦላይ ወታደራዊ ማሰልጠኛ በመላኩ የጣሳቸው ህጎች አሉ ትላለች።
"ተግባሩ በትንሹ አራት የህገ መንግስቱን አንቀፆች ይጥሳል።የታሰሩ ሰዎች መብት፣ የተከሰሱ ሰዎች መብት ፣ የተጠረጠሩ ሰዎች መብትና ከዚያም ጋር ተያይዞ መደረግ የሚገባቸው ነገሮች በትንሹ አንድ አራት የህገመንግስቱ አንቀፆች ተጥሰዋል። የወንጀል ስነስርዓት ህጉንም ብንመለከት እዚያ ላይም የተጣሱ ነገሮች አሉ" ትላለች።
እሷ እንደምትለው በመሰረተ ሃሳብ ደረጃ መንግስት ሰዎችን ሰብስቦ ካሰረ ያሰረበትን ምክንያት ፍርድ ቤት አቅርቦ ፍቃድ መጠየቅ ይኖርበታል። በወሰደው እርምጃ የቀማው የግለሰቦችን ነፃነት በመሆኑ ይህን ደግሞ ያለ ፍርድ ቤት ፍቃድ ማድረግ አይቻልም።
ስለዚህም ግለሰቦቹን ፍርድ ቤት አለማቅረብ፣ የተከሰሱበትን ምክንያት አለማወቃቸውን እንዲሁም የዋስትና መብታቸውን መነፈጋቸው በሃይማኖትና በዘመድ መጎብኘት አለመቻላቸውን የመሰሉ ነገሮች ሲታዩ በእርምጃው ብዙ የመብት ጥሰቶች እንዳሉ ታስረዳለች።
ምንጭ፦ BBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ከአዲስ አበባ ተወስደው ጦላይ ወታደራዊ ማሰልጠኛ የሚገኙ የአዲስ አበባ ወጣቶች በሳምንቱ መጨረሻ እንደሚለቀቁ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ብርጋዲየር ጄኔራል #ደግፌ_በዲ ለቢቢሲ ገለፁ።
ወጣቶቹ የተያዙት "በጎዳና ላይ ንብረት ሲያወድሙና ሁከት ሲፈጥሩ ነው" ያሉት ኮሚሽነሩ መጀመሪያ ከተያዙት ተጣርቶ አሁን በማሰልጠኛ ያሉት 1174 እንደሆኑ ገልፀዋል።
እሳቸው እንደሚሉት የፈፀሙት ተግባር በህግ የሚያስጠይቃቸው ቢሆንም መታነፅ እንዳለባቸው በማመን ለዚህም ከቤተሰብና ከማህበረሰብ ቀጥሎ ሃላፊነት ያለበት መንግስት በመሆኑ ይህን ተግባሩን እየተወጣ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
"ማነፅ ብቻ ሳይሆን የወጣቶቹን ማንነት በመገንዘብ ስራ የሌለው ስራ እንዲሰራ፣ ተማሪውም ትምህርቱን እንዲቀጥል ሁኔታዎችን ለማመቻቸት ነው እነዚህ ልጆች ላይ ስራ እየሰራን ያለነው"ብለዋል ኮሚሽነሩ።
ይህን ለማድረግ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደርን ጨምሮ የሚመለከታቸው ትብብር ላይ መሆናቸውንም ገልፀዋል።
የአዲስ አበባ ፖሊሶች ወጣቶችን በቡድን ሲደበድቡ የሚያሳይ ቪዲዮ ስለመለቀቁ ለኮሚሽነሩ ከBBC ጥያቄ ተነስቶላቸው ነበር።
ምንም እንኳ እሳቸው ተንቀሳቃሽ ምስሉን ባይመለከቱትም ቦታው ተገልፆ ትክክለኛ መረጃ ከደረሳቸው ተግባሩን በፈፀሙት አካላት ላይ ተጣርቶ #እርምጃ እንደሚወሰድ ገልፀዋል።
መሳለሚያ ሞቢል አካባቢ ለግንቦት ሰባት መሪዎች አቀባበል ሲደረግ ሰንደቅ አላማ በመስቀልና ባነሮችን በመለጠፍ ይንቀሳቀስ ነበር።
ያሳደጉትና የክርስትና ልጃቸው በአመፅ ሳይሆን የግንቦት ሰባት መሪዎች አቀባበል ላይ ባደረገው ተሳትፎ ከዚያም የቡራዮውን ግድያ በመቃወም ሰላማዊ ሰልፍ በመውጣቱ መታሰሩን አቶ ዘመነ ሞላ ለቢቢሲ ይገልፃሉ።
ከዚህ ውጭ ልጃቸው ሰላማዊ እንደሆነም ያስረዳሉ። ያሳደጉት ልጃቸው ወጣት ፍስሃ ደምስ የ25 ዓመት ወጣት ሲሆን እናቱ እንደሌለችና የሚኖረው ከአቅመ ደካማ አያቱ ጋር እንደነበር አቶ
ዘመነ ይናገራሉ።
እሳቸው እንደገለፁት የታሰረው ወደ ቤቱ የሚወስድ መንገድ ላይ አመሻሽ ላይ ነው። መጀመሪያ ወደ ተወሰደበት ፖሊስ ጣቢያ ሄደው ሲጠይቁ ጦላይ መወሰዱን መስማታቸውንና ከዚያ በኋላ ያለ ምንም መረጃ ቤተሰብ ስቃይ ላይ እንዳለ ይገልፃሉ።
የአዲስ አበባ ወጣቶች ጅምላ የመገናኛ ብዙሃንና የማህበራዊ ሚዲያ ርእሰ ጉዳይ ሆኖ ሰንብቷል። በማህበራዊ ሚዲያው የአዲስ አበባ ወጣቶች ይፈቱ የሚል ዘመቻም በመካሄድ ላይ ነው።
አምነስቲ ኢንተርናሽናል የአዲስ አበባ ወጣቶችን በጅምላ አስሮ ስልጠና ማስገባት የህግ አግባብነት እንደሌለው ባወጣው መግለጫ አስታውቋል።
የህግ ባለሙያና የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ፕሮጀክት ፕሮጀክት አስተባባሪ የሆነችው ሶሊያና ሽመልስ መንግስት እነዚህን ወታደሮች አስሮ ወደ ጦላይ ወታደራዊ ማሰልጠኛ በመላኩ የጣሳቸው ህጎች አሉ ትላለች።
"ተግባሩ በትንሹ አራት የህገ መንግስቱን አንቀፆች ይጥሳል።የታሰሩ ሰዎች መብት፣ የተከሰሱ ሰዎች መብት ፣ የተጠረጠሩ ሰዎች መብትና ከዚያም ጋር ተያይዞ መደረግ የሚገባቸው ነገሮች በትንሹ አንድ አራት የህገመንግስቱ አንቀፆች ተጥሰዋል። የወንጀል ስነስርዓት ህጉንም ብንመለከት እዚያ ላይም የተጣሱ ነገሮች አሉ" ትላለች።
እሷ እንደምትለው በመሰረተ ሃሳብ ደረጃ መንግስት ሰዎችን ሰብስቦ ካሰረ ያሰረበትን ምክንያት ፍርድ ቤት አቅርቦ ፍቃድ መጠየቅ ይኖርበታል። በወሰደው እርምጃ የቀማው የግለሰቦችን ነፃነት በመሆኑ ይህን ደግሞ ያለ ፍርድ ቤት ፍቃድ ማድረግ አይቻልም።
ስለዚህም ግለሰቦቹን ፍርድ ቤት አለማቅረብ፣ የተከሰሱበትን ምክንያት አለማወቃቸውን እንዲሁም የዋስትና መብታቸውን መነፈጋቸው በሃይማኖትና በዘመድ መጎብኘት አለመቻላቸውን የመሰሉ ነገሮች ሲታዩ በእርምጃው ብዙ የመብት ጥሰቶች እንዳሉ ታስረዳለች።
ምንጭ፦ BBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update⬆️የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት የአስፈጻሚ አካላትን ስልጣንና ተግባር ለመወሰን ያጸደቀው አዋጅ ቁጥር 1097/2011 መሰረት የተጠሪ ተቋማት ዝርዝር ከላይ ባለው ምስል ቀርቧል።
ምንጭ፦ አቶ ፍፁም አረጋ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ምንጭ፦ አቶ ፍፁም አረጋ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ገንዘብ #አጭበርባሪዎች ጥቆማ!
TechTalk With Solomon⬇️
"ገንዘብ #አጭበርባሪዎች ጥቆማ! በርካቶች በኢትዮጵያ እና በሌላም ቦታ ያሉ ሰዎች "እኛ አናደርግላችኋለን" በሚሉ አጭበርባሪዎች በኩል #የቢትኮይን ኢንቨስትመንት ውስጥ እየገቡ እንዳለ እየተነገረኝ ነው! አንድ ጠቃሚ ምክር ልስጣችሁ፤ ማንም ሰው ወደናንተ ቀርቦ ሃብታም አደርጋችኋለሁ እያለ ለፍታችሁ የሰራችሁትን ገንዘብ ለዚህ ጉዳይ ቢጠይቃችሁ ፍጹም እንዳታረጉት! ይህ በአሁን ሰዓት እየተበራከተ ያለ ወንጀል/#ማጭበርበር ነው።
"ሰዎች ብር ሲሰሩ እያየሁ ነው" ትሉ ይሆናል። ይህ አይነት ወንጀል #ከክሪፕቶከረንሲ በፊትም የነበረ ሲሆን፣ ነገሩ እንዲህ ነው -በኢንቨስትመንት ዓለም የሚታወት አንድ አደገኛ ወንጀል አለ "ፖንዚ ስኪም" ይባላል። ይህ ማለት ገንዘባችሁን በናንተ ስም ኢንቨስት አድርጌ #ትርፍ አመጣላችኋለሁ የሚለው አካል አብዛኛውን ገንዘብ ራሱ ከበላ በኋላ፣ ከአዲሲሶቹ ተጠቂዎች የሰበሰውን ለበፊቶቹ ተጠቂዎች በመስጠት በእርግጥ ትርፍ እያስገኘ እንዳለ ማስመሰል ነው። ከዚህ ወንጀል በጣም በጣም በጣም ተጠበቁ!
ክሪፕቶከረንሲ ላይ እጅግ በመጠኑ ኢንቨስት ማድረግ ከተፈለገ (አሁን ብዙም ባይመከርም) በትክክለኛ ሁኔታ እና በታወቁ አፖች (መተግበሪያዎች) በራሳችሁ ማድረግ ትችላላችሁ (ችግሩ በኢትዮጵያ የባንክ ካርድ አሰራር ማነስ እና እነዚህ አፖች ምናልባትም በኢትዮጵያ ላይሰሩ መቻላቸው ነው)"
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TechTalk With Solomon⬇️
"ገንዘብ #አጭበርባሪዎች ጥቆማ! በርካቶች በኢትዮጵያ እና በሌላም ቦታ ያሉ ሰዎች "እኛ አናደርግላችኋለን" በሚሉ አጭበርባሪዎች በኩል #የቢትኮይን ኢንቨስትመንት ውስጥ እየገቡ እንዳለ እየተነገረኝ ነው! አንድ ጠቃሚ ምክር ልስጣችሁ፤ ማንም ሰው ወደናንተ ቀርቦ ሃብታም አደርጋችኋለሁ እያለ ለፍታችሁ የሰራችሁትን ገንዘብ ለዚህ ጉዳይ ቢጠይቃችሁ ፍጹም እንዳታረጉት! ይህ በአሁን ሰዓት እየተበራከተ ያለ ወንጀል/#ማጭበርበር ነው።
"ሰዎች ብር ሲሰሩ እያየሁ ነው" ትሉ ይሆናል። ይህ አይነት ወንጀል #ከክሪፕቶከረንሲ በፊትም የነበረ ሲሆን፣ ነገሩ እንዲህ ነው -በኢንቨስትመንት ዓለም የሚታወት አንድ አደገኛ ወንጀል አለ "ፖንዚ ስኪም" ይባላል። ይህ ማለት ገንዘባችሁን በናንተ ስም ኢንቨስት አድርጌ #ትርፍ አመጣላችኋለሁ የሚለው አካል አብዛኛውን ገንዘብ ራሱ ከበላ በኋላ፣ ከአዲሲሶቹ ተጠቂዎች የሰበሰውን ለበፊቶቹ ተጠቂዎች በመስጠት በእርግጥ ትርፍ እያስገኘ እንዳለ ማስመሰል ነው። ከዚህ ወንጀል በጣም በጣም በጣም ተጠበቁ!
ክሪፕቶከረንሲ ላይ እጅግ በመጠኑ ኢንቨስት ማድረግ ከተፈለገ (አሁን ብዙም ባይመከርም) በትክክለኛ ሁኔታ እና በታወቁ አፖች (መተግበሪያዎች) በራሳችሁ ማድረግ ትችላላችሁ (ችግሩ በኢትዮጵያ የባንክ ካርድ አሰራር ማነስ እና እነዚህ አፖች ምናልባትም በኢትዮጵያ ላይሰሩ መቻላቸው ነው)"
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ወይዘሮ ዳግማዊት፦
".....የተጀመረውን ሃገራዊ ለውጥ ለማስቀጠል እንዲሁም ህዝባችንን #በታማኝነት እና #በቅንነት ለማገልገል ቃል እየገባሁ ሃገራችንን ከድህነት ለማላቀቅ በምናደርገው ጥረት ከጎናችን በመሆን የተለመድውን አስተዋጽኦ እንድታደርጉ በታላቅ አክብሮት እጠይቃለሁ።"
@TIKVAHETHIOPIA
".....የተጀመረውን ሃገራዊ ለውጥ ለማስቀጠል እንዲሁም ህዝባችንን #በታማኝነት እና #በቅንነት ለማገልገል ቃል እየገባሁ ሃገራችንን ከድህነት ለማላቀቅ በምናደርገው ጥረት ከጎናችን በመሆን የተለመድውን አስተዋጽኦ እንድታደርጉ በታላቅ አክብሮት እጠይቃለሁ።"
@TIKVAHETHIOPIA
#update ፌደራል ፖሊስ⬇️
በአዲስ አበባ ከጸጥታ ችግር ጋር ተያይዞ በቁጥጥር ስር ውለው በጦላይ ስልጠና ሲከታተሉ የቆዩ ወጣቶች በያዝነው ሳምንት #እንደሚለቀቁ ተገለፀ።
ወጣቶቹ ከመስከረም 2 እስከ መስከረም 8 2011 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ ከነበረው የፀጥታ ችግር ጋር ተያይዞ ነበር በቁጥጥር ስር የዋሉት።
የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጀነራል ዘይኑ ጀማል ለFBC እንደተናገሩት፥ በመንግስት በኩል በቁጥጥር ስር ለዋሉት ወጣቶቹ እስካሁን የተለያዩ ስልጠናዎችን ሲወስዱ ቆይተዋል።
በጦላይ ለአንድ ወር እራስን ከወንጀል ስለማራቅ እና ተያያዠ ስልጠናዎችን ለመስጠት የተያዘው የጊዜ ሰሌዳም የፊታችን #ሀሙስ ይጠናቀቃል ብለዋል ኮሚሽነር ጀነራል ዘይኑ ጀማል።
አስፈላጊው ሎጀስቲክስ ሚሟላ ከሆነ ወጣቶቹ የፊታችን ሀሙስ ካልሆነ ደግሞ እስከ መጪው ቅዳሜ ድረስ የሚለቀቁ መሆኑን ገልጸዋል።
አቶ ዘይኑ ወጣቶችን አስተምሮ ከመልቀቅ ባለፈ ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጋር በመነጋገር ስራ አጥ የሆኑትን በጥቃቅንና አነስተኛ አደራጅቶ ወደ ስራ ለማስገባት ዝግጅት መደረጉንም ተናግረዋል።
በከተማዋ በነበረው የጸጥታ ችግር በቁጥጥር ስር ውለው ስልጠና ሲከታተሉ የነበሩ 1 ሺ 204 ወጣቶች ሲሆኑ፥ ከነዚህ ውስጥ በወንጀል የተጠረጠሩት 83 ወጣቶች በህግ የሚጠየቁ ናቸው ብለዋል።
ምንጭ፦ fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በአዲስ አበባ ከጸጥታ ችግር ጋር ተያይዞ በቁጥጥር ስር ውለው በጦላይ ስልጠና ሲከታተሉ የቆዩ ወጣቶች በያዝነው ሳምንት #እንደሚለቀቁ ተገለፀ።
ወጣቶቹ ከመስከረም 2 እስከ መስከረም 8 2011 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ ከነበረው የፀጥታ ችግር ጋር ተያይዞ ነበር በቁጥጥር ስር የዋሉት።
የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ኮሚሽነር ጀነራል ዘይኑ ጀማል ለFBC እንደተናገሩት፥ በመንግስት በኩል በቁጥጥር ስር ለዋሉት ወጣቶቹ እስካሁን የተለያዩ ስልጠናዎችን ሲወስዱ ቆይተዋል።
በጦላይ ለአንድ ወር እራስን ከወንጀል ስለማራቅ እና ተያያዠ ስልጠናዎችን ለመስጠት የተያዘው የጊዜ ሰሌዳም የፊታችን #ሀሙስ ይጠናቀቃል ብለዋል ኮሚሽነር ጀነራል ዘይኑ ጀማል።
አስፈላጊው ሎጀስቲክስ ሚሟላ ከሆነ ወጣቶቹ የፊታችን ሀሙስ ካልሆነ ደግሞ እስከ መጪው ቅዳሜ ድረስ የሚለቀቁ መሆኑን ገልጸዋል።
አቶ ዘይኑ ወጣቶችን አስተምሮ ከመልቀቅ ባለፈ ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጋር በመነጋገር ስራ አጥ የሆኑትን በጥቃቅንና አነስተኛ አደራጅቶ ወደ ስራ ለማስገባት ዝግጅት መደረጉንም ተናግረዋል።
በከተማዋ በነበረው የጸጥታ ችግር በቁጥጥር ስር ውለው ስልጠና ሲከታተሉ የነበሩ 1 ሺ 204 ወጣቶች ሲሆኑ፥ ከነዚህ ውስጥ በወንጀል የተጠረጠሩት 83 ወጣቶች በህግ የሚጠየቁ ናቸው ብለዋል።
ምንጭ፦ fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከሁለት ሳምንት በኋላ ወደ ሶማሊያ #ሞቃዲሾ በረራ ይጀምራል። አየር መንገዱ በሳምንት ሶስት ጊዜ ሰኞ ረቡዕ
እና ዓርብ ወደ ሞቃዲሾ ለመብረር እቅድ ይዟል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
እና ዓርብ ወደ ሞቃዲሾ ለመብረር እቅድ ይዟል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia