TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
59.4K photos
1.51K videos
215 files
4.12K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ዱላ አታቀብሉ፤ አታጋግሉ!⬇️

የኦነግ አመራሮች አቀባበል #ያማረ እንዲሆን እና የኦነግ ደጋፊ የሆኑ ወንድሞች ደሥ እንዲላቸው ማገዝ #ተገቢ ነው። ከፀቡ በፊትም በሰከነ
መንገድ #ተነጋግሮ መግባባት መልመድ አለብን። አላሥፈላጊ የሆነ #ፉክክር እና #ብሽሽቅ አያሥፈልገንም።

ለወጣቱ ለባለፉት 27 ዓመታት ሲሰበክለት የኖረው #ልዩነት እንጅ ወንድማማችነት እና መተባበር አይደለም። ሥለዚህ በትንሽ ነገር ወደፀብ ለማምራት ቀላል ሆኗል። ጦር ለማወጅም ማሰላሰል አያሥፈልግም። #ሞባይልን ወጣ አድርጎ መተኮሥ ነው። ሃላፊነት የማይሰማው እና #ቢራ እየጠጣ "አትነሳም ወይ" የሚል ብዙ ነው። የእብድ ገላጋዩ እና ዱላ አቀባዩ የትየለሌ ነው። የሚመክር እና አንተም ተው፣ አንተም ተው የሚል ነው የሚያሥፈልገን። በዚህ የተነሳም ሰፊው መንገድ ይጠበናል። #የምንፈልገውን ባንዲራ ለመሥቀል ሌላውን ማውረድ ተገቢ አይደለም።

ሌሎችም የሚፈልጉትን እና #አርማየ ነው የሚሉትን ቢሰቅሉ የሌላውን #መብት እሥካልነኩ ድረሥ #መብታቸው ነው። ሥንተባበር ሁሉም #ቀላል ይሆናል። ሆደ ሰፊነት ያሥፈልጋል።

ፌሥቡክ ላይ የምታጋግሉ ሰከን በሉ!
.
.
ከዳንኤል ተፈራ (የቀድሞው የአንድነት ፓርቲ አመራር አባል)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ወገን! ሰከን ማለት ዋጋ አለው! #ሰላምን እስክታጣት ድረስ ምንም ላይስመስልህ ይችላል። ነገር ግን ሰላም አንዴ ከእጅህ ከወጣች የልጅ ልጅህን #ብትገብር እንኳን መልሰህ ላታገኛት ትችላለህ።

#ሶሪያ የቀደመው ገፅታዋን እና #አሁን ያለውን ገፅታዋን ከላይ ባለው ፎቶው ተመልከት። ያኔ በትንሽ በትልቁ አትባላም።

ሰላም ለኢትዮጵያ!
ተወያይተን ችግራችንን እንፍታ!
#ETHIOPIA

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ድሬዳዋ⬆️ለአርቲክስ እና አክቲቪስት ታማኝ በየነ በድሬዳዋ ከተማ ደማቅ አቀባበል እየተደረገለት ይገኛል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia